የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ2016 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርትን አጸደቀ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የከተማ አስተዳደሩን የ2016 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት እና የ2017 በጀት ዓመት የትኩረት አቅጣጫ ላይ ከተወያየ በኋላ አጽድቋል፡፡
ምክር ቤቱ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ያቀረቡትን የከተማ አስተዳደሩን የ2016 በጀት ዓመት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ነው ተወያይቶ በሙሉ ድምጽ ያጸደቀው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት 3ተኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ እንደሚገኝ የከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ አመላክቷል።