Fana: At a Speed of Life!

በሕገ-ወጥ መንገድ ነዳጅ ሲሸጡ ነበር የተባሉ 22 ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ዋሉ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 12፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሕገ-ወጥ መንገድ ነዳጅ በመደበቅ ሲሸጡ ነበር ያላቸውን 22 ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የሐረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

ግለሰቦቹ በሐረር ከተማ በሕገ-ወጥ መንገድ ነዳጅ ሲሸጡ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን በኮሚሽኑ የወንጀል ምርመራ ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር ረመዳን ጅብሪል ተናግረዋል፡፡

በሁሉም ወረዳዎች በተደረገው ጥናት 1 ሺህ 518 ሊትር በጄሪካን እና በፕላስቲክ ጠርሙሶች የተሞላ ነዳጅ ተይዟል ማለታቸውን የኮሚሽኑ መረጃ አመላክቷል፡፡

የነዳጅ ማደያዎችም በዚህ ሕገ-ወጥ የነዳጅ ንግድ እጃቸው እንዳለበት በመግለጽ በቀጣይ ተገቢው ማጣራት ከተደረገ በኋላ ሕጋዊ ርምጃ እንደሚወሰድ አረጋግጠዋል፡፡

የቁጥጥር እና ክትትል ሥራውም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ነው ያመላከቱት፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.