Fana: At a Speed of Life!

የመዲናዋ ነዋሪዎች በነገው የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 16፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች በነገው ሀገር አቀፍ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሐ-ግብር በነቂስ በመውጣት አረንጓዴ ዐሻራቸውን እንዲያኖሩ ጥሪ ቀረበ፡፡

የአሥተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት÷ “ውድ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ነገ በአንድ ጀምበር በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚከናወነው ችግኝ ተከላ በመሳተፍ ተደማሪና ተጨማሪ ድል በጋራ እናስመዝግብ” ብለዋል፡፡

በነቂስ ወጥተን እንትከል፤ ለመጪው ትውልድ ዐሻራ እናስቀምጥ ሲሉም ጥሪ አቀርበዋል፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.