Fana: At a Speed of Life!

ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ኩንታል በላይ ምርት ተሰበሰበ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡የግብርና ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት ያለፉት ዘጠኝ ወራት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ነው፡፡

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) እንዳሉት÷በበጀት ዓመቱ 30 ሚሊየን ሄክታር በዘር በመሸፈን ከ1 ነጥብ 4 ቢሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቅዷል።

ባለፉት ዘጠኝ ወራትም 31 ነጥብ 6 ሚሊየን ሄክታር በዘር መሸፈኑን ጠቅሰው÷ በዚህም እስካሁን ከ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ኩንታል በላይ ምርት መሰብሰቡን ተናግረዋል፡፡

1 ነጥብ 1 ሚሊየን ቶን ቡና መመረቱን የገለጹት ሚኒስትሩ÷300 ሺህ ኩንታል ቡና ለውጪ ገበያ በማቅረብ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር ገቢ መገኘቱን ጠቁመዋል፡፡

እስካሁን ከ300 ሚሊየን ኩንታል በላይ የስንዴ ምርት መሰብሰቡን ገልጸው÷የበጋ መስኖ ስንዴን የመሰብሰቡ ሒደት አለመጠናቀቁን አመልክተዋል፡፡

ባለፉት ዘጠኝ ወራት የግብርናው ዘርፍ በምርታማነት እና እሴት በመጨመር ረገድ የተመዘገበው ውጤት ከፍተኛ እድገት ያሳየ መሆኑን ሚኒስትሩ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በይስማው አደራው

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.