Fana: At a Speed of Life!

የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን ሊቀመንበር ማህሙድ አሊ ዩሱፍ ከሶማሊያ ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይቱ ወቅት ሊቀመንበሩ፤ የሶማሊያን የሰላም መንገድ ለመደገፍ ህብረቱ ያለውን ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።

ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ በበኩላቸው ለተደረገላቸው ደማቅ አቀባበል እና የአፍሪካ ህብረት ቀጣይ ድጋፍ አድናቆታቸውን መግለጻቸውን የህብረቱ መረጃ አመላክቷል።

ኢትዮጵያ ከጣሊያን እና ከተባበሩት መንግስታት ጋር በመተባበር ያዘጋጀችው ሁለተኛው የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ላይ የታደሙት የሶማሊያ ፕሬዚዳንት በጉባኤው፤ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ዓለም አንድ ላይ የሚቆምበት ወቅት መሆኑን አንስተዋል።

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/@fanamcdocumentary በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.