Fana: At a Speed of Life!

ከንቲባ አዳነች አቤቤ የቦሌ ቅርንጫፍ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ስራ አስጀመሩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ የቦሌ ቅርንጫፍ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን መርቀው ስራ አስጀምረዋል።

ከንቲባዋ በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ሕዝቡ ሲጠይቅና ቅሬታ ሲያቀርብበት የነበረውን የአገልግሎት ዘርፍ ለማዘመን ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

ለዚህም በመዲናዋ ጳጉሜን 5 ቀን 2017 ዓ.ም ከተጀመረው መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በተጨማሪ በሌሎች ክፍለ ከተሞች የማስፋፋት ስራ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ዛሬ የተመረቀው የቦሌ ቅርንጫፍ የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትም የዚህ ማሳያ ነው ብለዋል።

በመዲናዋ አሁን ላይ 107 አገልግሎቶች ዲጂታላይዝ ተደርገው ሕዝቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኝ መደረጉን ጠቁመዋል።

የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በጥራትና ቴክኖሎጂ የተሻለ መሆኑን የጠቆሙት ደግሞ የኢትዮጵያ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) ናቸው።

የቦሌ አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ባለስድስት ወለል ህንጻ በአራት ወራት ውስጥ ተገንብቶ የተጠናቀቀ ሲሆን÷ አሁን ላይ 12 ተቋማት በድምሩ 96 አገልግሎቶችን መስጠት መጀመራቸው ተገልጿል።

በታሪኩ ለገሰ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.