Fana: At a Speed of Life!

ክርስቲያኖ ሮናልዶ የመጀመሪያው የእግር ኳስ ቢሊየነር ሆነ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፖርቹጋላዊው ኮከብ ክርስቲያኖ ሮናልዶ የመጀመሪያው የእግር ኳስ ቢሊየነር ሆኗል፡፡

የአምስት ጊዜ የባሎንዶር አሸናፊው ክርስቲያኖ ሮናልዶ የተጣራ የሀብት መጠን 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ዶላር መድረሱን የብሉምበርግ ዘገባ አመላክቷል፡፡

ተጨዋቹ ከሳዑዲው ክለብ አል ናስር የሚያገኘው 300 ሚሊየን ፓውንድ ክፍያ እና ከሌሎች አጋሮች የሚያገኘው ገቢ ያለውን የሀብት መጠን ከፍ እንዳደረገለትም ነው የተገለጸው፡፡

በዚህም ክርስቲያኖ ሮናልዶ በብሉምበርግ የቢሊየነሮች ደረጃ ውስጥ መካተት የቻለ የመጀመሪያው የእግር ኳስ ተጨዋች መሆን ችሏል።

ሮናልዶ ከፖርቹጋል እግር ኳስ ፌዴሬሽን የምንጊዜም ምርጡ ተጨዋች በመባል በትናንትናው ዕለት የክብር ሽልማት እንደተሰጠው ይታወሳል፡፡

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-

YouTube www.youtube.com/@fanamediacorporation
Facebook www.facebook.com/fanabroadcasting
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/@fana_television
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/@fanaentertainment
Facebook www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate
TikTok www.tiktok.com/@fanamc_entertainment
Amharic Podcast YouTube www.youtube.com/@fanamcpodcast በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.