Fana: At a Speed of Life!

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በስሎቬኒያ ሉብሊያ ማራቶን አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በስሎቬኒያ ሉብሊያ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታ አሸንፈዋል፡፡

በወንዶች በተደረገው ውድድር አትሌት ሃፍታሙ አባዲ 2 ሰዓት ከ 06 ደቂቃ ከ52 ሰኮንድ በመግባት ውድድሩን በበላይነት አጠናቅቋል።

በውድድሩ ላይ የተሳተፈው ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ከማል ሁሴን ሦስተኛ  ደረጃን በመያዝ ውድድሩን ጨርሷል፡፡

በሴቶች ደግሞ አትሌት ትዕግስት ገዛኸኝ 2 ሰዓት ከ22 ደቂቃ ከ46 ሰኮንድ በመግባት ነው ውድድሯን በአንደኝነት ያጠናቀቀችው፡፡

You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.