Fana: At a Speed of Life!

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መግለጫ ዋና ዋና ነጥቦች፡-

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሒሩት ገ/ሥላሴ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን አሁናዊ ሁኔታ አስመልክተው በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
ምክትል ዋና ኮሚሽነሯ በመግለጫቸው ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች እንደሚከተለው ቀርበዋል፡-
👉 ባለፉት ቀናት ስምንቱ የአጀንዳ ቡድኖች እያንዳንዳቸው 16 ተመካካሪዎችን መርጠው ከየቡድኑ የቀረቡ ምክረ ሀሳቦችን ለማጣጣም ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡
👉 ይህ የማጣጣም ስራ በምክረ ሀሳቦች ውስጥ ተቃርኖ እና ድግግሞሽን በማስቀረት ወጥ በሆነ መንገድ እንዲቀርቡ የሚያስችል ነው፡፡
👉 በተጨማሪም የየቡድኖቹ ተወካዮች በሌሎች ቡድኖች ስለቀረቡ ምክረ ሀሳቦች ግንዛቤ ይወስዳሉ፤ እርስ በርስ ይመካከራሉ፡፡
👉 ካሳለፍነው ሀሙስ ጀምሮ ሲከናወን የቆየው ምክረ ሀሳቦችን የማጣጣም ስራ ወሳኝ ስራ ነው፡፡
👉 የምክረ ሀሳብ ማጣጣም ስራው በዛሬው ዕለት ይጠናቀቃል፡፡
👉 ተጣጣመው የሚቀርቡ የስምንቱም ቡድኖች ምክረ ሀሳቦች ለሁሉም ተመካካሪዎች ተመልሰው ይቀርባሉ፡፡
👉 ስምንቱ ቡድኖች የራሳቸውን ምክረ ሀሳብ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም ቡድኖች ያቀረቧቸውን ምክረ ሀሳቦች ይተዋወቃሉ፤ ግብአት እንዲሰጡ ይደረጋል፡፡
👉 እያንዳንዱ ቡድን በሌሎች ቡድኖች ምክረ ሀሳብ ላይ የሚሰጡት ግብአት ተሰብስቦ የመጨረሻው ሰነድ ይዘጋጃል፡፡
👉 ስምንቱም ቡድኖች ኢትዮጵያን የሚመስሉ ቡድኖች ናቸው፤ በሁሉም ቡድኖች ውስጥ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ይገኛሉ፤ ሁሉም የኢትዮጵያ ወረዳዎች በስምንቱም ቡድኖች ውስጥ ተወክለዋል፡፡
👉 ዛሬ ከሰዓት በኋላ እና ነገ በምክረ ሀሳቦቹ ላይ ግብአት ከተሰበሰበ በኋላ ከነገ በስቲያ ረቡዕ ዕለት ሁሉም ተመካካሪዎች ያጸድቁታል፡፡
👉 በሒደቶቹ ላይ እየቀረቡ ያሉ ቅሬታዎችን እየመረመርን ውሳኔ እየሰጠን ነው፤ ቅሬታ በቀረበባቸው ቀሪ ጉዳዮች ላይም ውሳኔ እየሰጠን እንቀጥላለን፡፡
👉 ቅሬታዎችን የሚያስተናግድ ኮሚቴ አለ፤ ኮሚቴው አጥንቶ ለኮሚሽነሮች ካውንስል ያቀርባል፤ ካውንስሉ ይወስናል፡፡
👉 በአንዳንድ ወቅት በራሳቸው መግለጫ ያወጡ ወገኖች አሉ፤ የምክክሩ መንፈስ መመካከር ነው፡፡
👉 የተጠናቀሩት ምክረ ሀሳቦች ጉባኤው የተስማማባቸው ጉዳዮች ናቸው፡፡
👉 በየትኛውም ሀገር በሚደረጉ ሀገራዊ ምክክሮች ሙሉ በሙሉ በሁሉም ጉዳዮች ላይ ይስማማሉ አይባልም፡፡
👉 በሀገራችን የተካሄደው የሀገራዊ ምክክር በአብዛኛው ጉዳይ ላይ እየተስማማ ጨርሷል፤ በአብዛኛው ጉዳይ ላይ ተግባብቷል፤ ስለዚህ ደስ ብሎናል፡፡
👉 የደረስንበትን ምዕራፍ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እናበስራለን፡፡
👉 የፈለግነውን መግባባት፤ የፈለግነውን ሰላም ያመጣልናል ብለን እንገምታለን፡፡
በኃይለማሪያም ተገኝ
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.