በመተከል ዞን ሲስለጥኑ የነበሩ የሚሊሻ አባላት ተመረቁ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የመተከልን ሰላም ለመመለስ ሲስለጥኑ የነበሩ 265 የሚሊሻ አባላት ዛሬ ተመረቁ ።
በአካባቢው የሚገኛው ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ኮ/ል መልካሙ በየነ መከላከያ ሰራዊት እና በፌዴራል ፖሊስ አማካኝነት ህብረተሰቡ ራሱን እንዲከላከል እና ፀረ ሰላም ሃይሎችን ለህግ አሳልፎ እንዲሰጥ አስፈላጊው ወታደራዊ ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል ።
የግልገል በለስ ከተማ ከንቲባ አቶ ሃብታሙ ውቧልታ በበኩላቸው ፥ ከአሁን በኋላ በዞናችን ምንም አይነት የሰላም ችግር እንዳያጋጥመን ሁላችንም በቆራጥነት በመታገል የሽብርተኛውን ስራ የሚያስፈፅሙ ፀረ ሰላም ሃይሎች ማጥፋት አለብን ብለዋል ።
በምርቃት ስነ ስርዓቱ ላይ የክልሉ ምክትል አፈጉባኤ ወ/ሮ አለምነሽ ይባስ ፣ የመተከል ዞን ምክትል ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጸሃይ ጉዮ፥ ከፍተኛ አመራሮችና የጦር መኮንኖች መገኘታቸውን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!