Fana: At a Speed of Life!

ሪያል ማድሪድ በሰፊ የግብ ልዩነት በአትሌቲኮ ማድሪድ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በጉጉት ሲጠበቅ በነበረው የማድሪድ ደርቢ ሪያል ማድሪድ በአትሌቲኮ ማድሪድ 5 ለ 2 በሆነ ውጤት ተሸንፏል፡፡ የአትሌቲን የማሸነፊያ ግቦች ለኖርማንድ፣ ሶርሎት፣ ሁሊያን አልቫሬዝ (2) እና አንትዋን ግሪዝማን አስቆጥረዋል፡፡ የሪያል…

ሊቨርፑል በክሪስታል ፓላስ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ6ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሊቨርፑል በክሪስታል ፓላስ 2 ለ 1 ተሸንፏል፡፡ የክሪስታል ፓላስን የማሸነፊያ ግቦች ኢስማኤላ ሳር እና ኤዲ ንኬቲያህ ከመረብ አሳርፈዋል፡፡

ማንቼስተር ሲቲ ድል ሲቀናው ቼልሲ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ6ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ማንቼስተር ሲቲ በርንሌይን ሲያሸንፍ ቼልሲ በብራይተን ሽንፈት አስተናግዷል፡፡ ኢቲሃድ ስታዲየም ላይ በተደረገው ጨዋታ ሲትዝኖቹ በርንሌይን 5 ለ 1 ሲያሸንፍ ÷ ግቦቹን እስቲቭ በራሱ…

የጸጥታው ም/ቤት በኢራን ላይ በድጋሚ ማዕቀብ ጣለ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት ከኒውክሌር ፕሮግራም ጋር በተያያዘ በኢራን ላይ በድጋሚ ኢኮኖሚያዊና ወታደራዊ ማዕቀብ ጥሏል፡፡ ምክር ቤቱ በፈረንጆቹ 2015 ስምምነት መሠረት በኢራን ላይ ተነስቶ የነበረው ማዕቀብ ነው በድጋሚ…

ኑኖ እስፕሪቶ ሳንቶ የዌስትሃም ዩናይትድ አሰልጣኝ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ግራሃም ፖተርን ያሰናበተው የለንደኑ ክለብ ዌስትሃም ዩናይትድ ፖርቹጋላዊውን አሰልጣኝ ኑኖ እስፕሪቶ ሳንቶን ሾሟል፡፡ በቅርቡ ከኖቲንግሃም ፎረስት የተሰናበተው ኑኖ የሶስት ዓመት ኮንትራት ለዌስትሃም ዩናይትድ መፈረሙን ክለቡ አስታውቋል፡፡…

ማንቼስተር ዩናይትድ በብሬንትፎርድ ተሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 6ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወደ ለንደን ያቀናው ማንቼስተር ዩናይትድ በብሬንትፎርድ 3 ለ 1 ተሸንፏል፡፡ የብሬንትፎርድን የማሸነፊያ ግቦች ኢጎር ቲያጎ (2) እና ማቲያስ የንሰን ከመረብ አሳርፈዋል፡፡…

የመስቀል ደመራ የኢትዮጵያውያን አንድነት ደምቆ የሚታይበት ልዩ የአደባባይ በዓል ነው – የተለያዩ ሀገራት ዜጎች

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የመስቀል ደመራ የኢትዮጵያውያን አንድነት ደምቆ የሚታይበት ልዩ የአደባባይ በዓል ነው አሉ በበዓሉ አከባበር ላይ የታደሙ የተለያዩ ሀገራት ዜጎች ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በአደባባይ የሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ትናንት…

“ጋሪ ዎሮ” የዘመን መለወጫ በዓል ማሕበራዊ መስተጋብር የሚጠናከርበት ነው – አቶ አሻድሊ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የቦሮ ሽናሻ "ጋሪ ዎሮ" የዘመን መለወጫ በዓል ይቅር ባይነትና ማሕበራዊ መስተጋብር የሚጠናከርበት ነው አሉ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሃሰን። የቦሮ ሽናሻ የዘመን መለወጫ በዓል "ጋሪ ዎሮ" በአሶሳ ከተማ በፓናል ውይይት…

ዌስትሃም ዩናይትድ አሰልጣኝ ግራሃም ፖተርን አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 17፣2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የለንደኑ ክለብ ዌስትሃም ዩናይትድ አሰልጣኝ ግራሃም ፖተርን ከኃላፊነታቸው አሰናብቷል፡፡ አሰልጣኙ ባለፈው የውድድር ዓመት አጋማሽ ክለቡን ከተረከቡ ወዲህ በቆይታቸው ካደረጉት 25 ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻሉት ስድስቱን ብቻ ነው፡፡…

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዳዲስ ሹመት ሰጠ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የተለያዩ ሹመቶችን ሰጥቷል። በዚህም መሰረት አቶ ሐፍታይ ገብረእግዚያብሔር የኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ፣ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ የቄራዎች ድርጅት ስራ አስኪያጅ፣ አቶ ዋለልኝ ደሳለኝ የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ…