Fana: At a Speed of Life!

አቶ ደመቀ መኮንን ከታንዛንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከታንዛንያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጃንዋሪ ማካምባ ጋር በስልክ ተወያይተዋል፡፡ ሚኒስትሮቹ በውይይታቸው በኢትዮጵያ እና ታንዛኒያ ቀጣናዊ የጋራ ፍላጎት ዙሪያ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ…

ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች ትምህርት ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ከተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የትምህርት ሚኒስትር አህመድ ቤልሁ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ውይይቱ በፓሪስ እየተካሄደ ከሚገኘው 42ኛው የዩኔስኮ ጠቅላላ ኮንፈረንስ ጎን ለጎን ነው የተደረገው፡፡ በዚህም…

የሴቶችን አቅም ማጎልበት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ከተባበሩት መንግስታት የሴቶች የኢትዮጵያ ተወካይ ሴሲል መኩሩቡጋ ጋር ተወያይተዋል። በውይይታቸውም በሥርዓተ ጾታ እኩልነት እና የሴቶችን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ…

ጋዛ ውስጥ የተፈጠረው የነዳጅ እጥረት በእንስሳት የሚጎተቱ ጋሪዎች በስፋት ለመጓጓዣነት እንዲውሉ አድርጓል

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በእስራኤልና ሃማስ ጦርነት የተነሳ ጋዛ ውስጥ የተፈጠረው የነዳጅ እጥረት በእንስሳት የሚጎተቱ ጋሪዎችን በስፋት ለመጓጓዣነት እንዲውሉ እያደረገ መሆኑ ተመላክቷል። በጋዛ አሁን ላይ የጭነት እንስሳት ጋሪ ሲጎትቱና ሰው ሲያመላልሱ እንዲሁም እቃ…

የዓለም ባንክ ለሀገር ውስጥ ገቢ አሰባሰብ እድገት የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያጠናክር አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም ባንክ በኢትዮጵያ ከሀገር ውስጥ የሚሰበሰበውን ገቢ ለማሳደግ በሚደረገው ጥረት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጿል፡፡ የገቢዎች ሚኒስቴር እና የዓለም ባንክ ልዑካን ቡድን ከሀገር ውስጥ የሚሰበሰበውን ገቢ ለማሳደግ የሚያስችል…

የስልክ መስመሮችን ከቴሌ እውቅና ውጪ በመጠቀም የተጠረጠረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ዋለ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሕገወጥ የስልክ መስመሮችን ከቴሌ እውቅና ውጪ ሲጠቀም ነበር በሚል የተጠረጠረ ግለሰብ ከነ እቃው በቁጥጥር ስር መዋሉን የሐረሪ ፖሊስ ኮሚሽን ወንጀል ምርመራ ዘርፍ አስታወቀ። በሐረሪ ክልል ድሬ ጠያራ ወረዳ ውስጥ አንድ ግለሰብ በሕገወጥ መንገድ…

ሳፋሪኮም በግማሽ ዓመት 34 ነጥብ 2 ቢሊየን የኬኒያ ሽልንግ የተጣራ ትርፍ አገኘ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 29፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሳፋሪኮም በግማሽ ዓመት 34 ነጥብ 2 ቢሊየን የኬኒያ ሽልንግ የተጣራ ትርፍ ማኝኘቱን አስታወቀ፡፡ የኬንያው ኩባንያ ጠንካራ ሆኖ እንደቀጠለ የገለጸ ሲሆን፥ በግማሽ ዓመቱ የ10 ነጥብ 9 በመቶ የገቢ እድገት በማስመዝገብ በአጠቃላይ 41 ነጥብ 6…

ለፓኪስታን ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ትልቅ እድል አለ – አምባሳደር ሚያን አቲፍ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፓኪስታን አምባሳደር ሚያን አቲፍ ለሀገራቸው ባለሃብቶች በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ ትልቅ እድል እንዳለ ተናገሩ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር ምስጋኑ አርጋ በኢትዮጵያ የፓኪስታን አምባሳደር ሚያን አቲፍ ሸሪፍን ዛሬ በጽህፈት…

299 ሺህ 990 ኩንታል ዩሪያ ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ ደረሰ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን በ2ኛው ዙር ለ2016/17 የምርት ዘመን ከውጭ የገዛው 299 ሺህ 990 ነጥብ 3 ኩንታል ዩሪያ ማዳበሪያ ጅቡቲ ወደብ መድረሱን አስታወቀ። ከ10 ቀናት በፊት 514 ሺህ 200 ኩንታል ዩሪያ የጫነች…

የአሜሪካ ጦር ተተኳሽ ለመግዛትና የጦር መሳሪያ ለማምረት 3 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር እንደሚያስፈልገው ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ ጦር ተተኳሽ መሳሪያዎችን ለመግዛትና የጦር መሳሪያዎችን ለማምረት 3 ነጥብ 1 ቢሊየን ዶላር የሀገሪቱ ኮንግረስ እንዲያጸድቅለት ጠየቀ፡፡ አሜሪካ የተለያዩ ጦር መሳሪያዎችን ወደ ዩክሬን እና አሁን ደግሞ ለእስራኤል እየላከች መሆኑ መረጃው…