Fana: At a Speed of Life!

ግብርናችን ለማዘመን በምናደርገው ጥረት የውሃና ኢነርጂ ግብዓት ወሳኝ ነው-ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ግብርናን ለማዘመን እና ለማሻገር በምናደርገው ጥረት የውሃና ኢነርጂ ግብዓት ወሳኝ ነው ሲሉ የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ በግብርና ሚኒስትሩ የተመራው የግብርና ሚኒስቴር አመራሮች ቡድን የውሃና ኢነርጂ አውደ ርዕይን…

የአፍሪካ ህብረት አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፎረም በመጪው መስከረም ወር ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 26፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) 2ኛው የአፍሪካ ህብረት አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ዓመታዊ ፎረም የፊታችን መስከረም ወር በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የአፍሪካ ህብረት አስታውቋል፡፡ በጀማሪ ስራ ፈጣሪዎች ላይ ያተኮረው ፎረሙ÷በተለይም የአፍሪካ ወጣቶች በክህሎት እና…

የአማራ ክልል መሥተዳድር ምክር ቤት የበጀት ድጋፍ ረቂቅ ላይ እየተወያየ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ክልል መሥተዳድር ምክር ቤት በ2016 በጀት ዓመት የበጀት ድጋፍ ረቂቅ እና ሌሎች አጀንዳዎች ላይ እየተወያየ ይገኛል፡፡ ከሰሞኑ የአማራ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፤ 2ኛ ዓመት የሥራ ዘመን፤ 1ኛ አስቸኳይ ጉባዔውን ሲያካሂድ በክልሉ ርእሰ…

በጆሃንስበርግ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ60 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተሰማ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ህንፃ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ60 በላይ ሰዎች መሞታቸው ተሰምቷል፡፡ በአደጋው ከ40 በላይ ሰዎችም ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸው የተገለጸ ሲሆን በከተማዋ መሀል የሚገኝ ህንፃ መውደሙ ነው የተገለፀው፡፡ የደቡብ…

ሩሲያ በማሊ ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲራዘም በፈረንሳይ የቀረበውን የውሳኔ ሃሳብ ተቃወመች

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በማሊ ላይ የተጣለው ማዕቀብ እንዲራዘም ፈረንሳይ ለተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተመድ) ያቀረበችውን የውሳኔ ሃሳብ ሩሲያ ውድቅ አድርጋለች፡፡ በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር ማሊ ወታደራዊ ጁንታ በሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ባቦከር ኬታ መፈንቅለ መንግስት…

አምባሳደር ምሥጋኑ ከዓለም የምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ተወካይ ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ምሥጋኑ አርጋ ከዓለም የምግብ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ተወካይ ክሪስ ኒኮይ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም የዓለም ምግብ ፕሮግራም በኢትዮጵያ በተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ ጉዳት ለደረሰባቸው ዜጎች እያደረገ…

ንግድ ባንክ በምስራቅ አፍሪካ የቻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን በምስራቅ አፍሪካ የቻምፒየንስ ሊግ ማጣሪያ 2ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቋል፡፡ በውድድሩ ፍፃሜ የታንዛኒያውን ጀኬቲ ኩዊንስ የገጠመው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ÷ መደበኛ ጨዋታውን በአቻ ውጤት ማጠናቀቁን…

ከሲንጋፖር የኢኮኖሚ ልማት ቦርድ አመራር ጋር ውይይት ተደረገ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢንቨስትመንት ኮሚሽን ከሚሽነር ሌሊሴ ነሚ እና የኢንዱስትሪ ፓርኮች  ኮርፖሬሽን ስራ አስፈጻሚ አክሊሱ ታደሰ ከሲንጋፖር የኢኮኖሚ ልማት ቦርድ አመራር ቡድን ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም÷ የሁለቱ ተቋማት አመራሮች…

ከዓለም የተፈጥሮ ሃብት ኢንስቲትዩት ጋር በትብብር ለመስራት ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የፕላንና ልማት ሚኒስትር ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ከዓለም የተፈጥሮ ሃብት ኢንስቲትዩት ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል፡፡ ፍጹም አሰፋ (ዶ/ር) ÷ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል እየወሰደች ያለውን እርምጃ አጠናክራ እንደምትቀጥል ገልፀዋል፡፡…

በወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፍቃድ አገልግሎት 56 ሚሊየን ዜጎችን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 22፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2015 በጀት ዓመት በወሰን ተሻጋሪ የወጣቶች በጎ ፍቃድ አገልግሎት ከ56 ሚሊየን በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ያደረጉ ተግባራት መከናወናቸውን የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ። የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር  ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)÷…