Fana: At a Speed of Life!

በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ታጣቂዎች 900 እስረኞችን አስለቀቁ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ቤኒ ከተማ ታጣቂዎች 900 እስረኞችን ማስለቀቃቸው ተገለፀ። ከካንግባዩ እስር ቤት ካመለጡት 900 እስረኞች መካከል የታጣቂ ቡድን አባላት እንደሚገኙበት ቢቢሲ የከተማዋን ከንቲባ ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።…

ዓለም አቀፉ የትምህርት ጉባኤ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ በዓለም አቀፉ የትምህርት ጉባኤ ላይ በበይነ መረብ እየተሳተፉ ነው፡፡ ጉባኤው በጋና፣ የኖርዌይ፣ እንግሊዝ እና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ ሳይንስና ባህል ማዕከል (ዩኔስኮ) በ ጋራ…

በአንድ ወር ከ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ላይ የመኪና እና የመኖሪያ ቤት ሽያጮች በባንክ በኩል ተፈጽመዋል

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በገዥና ሻጭ መካከል የሚደረገው የገንዘብ ቅብብል በባንክ በኩል ብቻ መሆኑን ተከትሎ ከ2 ነጥብ 8 ቢሊየን ብር ላይ የመኪና እና የመኖሪያ ቤት ሽያጮች በባንክ በኩል መፈፀማቸውን የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡ ኤጀንሲዉ…

በአዳማ ከተማ ህንጻ ተደርምሶ የአራት ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዳማ ከተማ ህንጻ ተደርምሶ ባደረሰው አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ። የከተማዋ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ ኢንስፔክተር ወርቅነሽ ገልሜቻ ለኢዜአ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው በከተማው ደምበላ ክፍለ…

የተለያዩ ተቋማት ለገበታ ለሃገር ድጋፍ እያደረጉ ነው

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የተለያዩ ድርጅቶች እና ተቋማት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ለገበታ ለሀገር ያቀረቡትን ጥሪ ተከትሎ ድጋፍ እያደረጉ ነው፡፡ በዚህም ሰባት ተቋማት በሶስተኛ ዙር ለገበታ ለሃገር ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ተቋማቱም፦ አዋሽ ባንክ - 30…

ኢትዮጵያ እና ሩሲያ በትምህርቱ ዘርፍ የሚያደርጉት ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገለፀ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ በኢትዮጵያ ከሩሲያ አምባሳደር ኢቭጌት ተረኪን ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም በሁለቱ ሀገራት መካከል ባለው የጋራ ኮሚሽን ጉዳይ እና በዚህ ዓመት በኢትዮጵያ በሚካሄደው የሃገራቱ የጋራ ኮሚሽን…

አውስትራሊያ፤ አሜሪካ፣ ጃፓን እና ህንድ የሚያደርጉትን ወታደራዊ ልምምድ ተቀላቀለች

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አውስትራሊያ ቻይና በልዩ ትኩረት የምትከታተለውን እና አሜሪካ፣ ጃፓን እና ህንድ በቤንጋል የባህር ዳርቻ የሚያካሂዱትን ወታደራዊ ልምምድ ተቀላቀለች። አውስትራሊያ ከፈረንጆቹ 2017 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የምትቀላቀለው እና ሀገራቱ ህዳር ወር…

በኢትዮጵያ በኮቪድ 19 ከሚያዙ ሰዎች ውስጥ 15 በመቶ የሚሆኑት ወደ ጽኑ ህሙማን ክፍል ይገባሉ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ አሁን ላይ በኮቪድ 19 ከሚያዙ ሰዎች ውስጥ 14 ነጥብ 9 በመቶዎቹ ወደ ጽኑ ህሙማን ክፍል እንደሚገቡ ተገለጸ። በኢትዮጵያ የኮቪድ19 ስርጭት ያለበት ሁኔታ እና ከመነሻው ጀምሮ እስካሁን ን ምላሽ በተመለከተ ለመገናኛ…

በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ከ90 ሺህ አለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 10፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር ከ90 ሺህ አልፏል። ባለፉት 24 ሰዓታትም ውስጥ በተደረገው 6 ሺህ 602 የላብራቶሪ ምርመራ 630 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል። በአጠቃላይ በኢትዮጵያ…

ዶናልድ ትራምፕ ሱዳንን አሸባሪነትን ከሚደግፉ ሃገራት ዝርዝር ውስጥ ሊሰርዟት ነው

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሱዳንን አሸባሪነትን ከሚደግፉ ሃገራት ዝርዝር ውስጥ ሊሰርዟት ነው፡፡ ፕሬዚዳንቱ ይህ የሚሆነው ግን ሱዳን በፈረንጆቹ1998 በኬንያ እና ታንዛኒያ በአሜሪካ ኤምባሲዎች ላይ በተፈጸመው ጥቃት ለተጎዱ እና…