Fana: At a Speed of Life!

“መስፈርት አላሟሉም” የተባሉ 41 ትምህርት ቤቶች ፈቃድ ተሠረዘ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) “የሚጠበቅባቸውን መስፈርት አላሟሉም” የተባሉ 41 ትምህርት ቤቶች ፈቃድ መሠረዙን የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር የትምህርትና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ ፈቃዳቸው የተሠረዘው የትምህርት ፖሊሲውን ባለመጠበቅና መስፈርቱን…

በክልሉ የመጀመሪያው የሣይንስና የፈጠራ ሥራዎች ዐውደ-ርዕይ ተከፈተ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የመጀመሪያ የሆነው የሣይንስና የፈጠራ ሥራዎች ዐውደ-ርዕይ ተከፈተ፡፡ በታርጫ ከተማ የተከፈተው የመምህራንና የተማሪዎች የሣይንስና የፈጠራ ሥራዎች ዐውደ-ርዕይ ለሁለት ቀናት እንደሚቆይ መገለጹን የክልሉ…

በአውሮፓ ዋንጫ ፈረንሳይ ከኦስትሪያ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 17ኛው የ2024 የአውሮፓ ዋንጫ መርሐ-ግብሮች ሲቀጥሉ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡ በዚሁ መሠረት በምድብ አምስት የሚገኙት ሮማንያ እና ዩክሬን ቀን 10 ሠዓት እንዲሁም ቤልጂየም ከስሎቫኪያ ምሽት 1 ሠዓት ላይ ይጫወታሉ፡፡ በሌላ በኩል…

አቶ እንዳሻው የ #ጽዱኢትዮጵያ ንቅናቄን በሆሳዕና ከተማ አስጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው "ጽዱ ከተሞች ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ሃሳብ የ #ጽዱኢትዮጵያ ንቅናቄን በሆሳዕና ከተማ አስጀምረዋል፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ በማስጀመሪያ መርሐ ግብሩ ላይ እንዳሉት÷ አካባቢን ፅዱና…

ዴንማርክና ስሎቬኒያ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀርመን አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው 17ኛው የ2024 የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታ ዴንማርክ እና ስሎቬኒያ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ የዴንማርክን ጎል ክርስቲያን ኤሪክሰን በ17ኛው ደቂቃ ከመረብ ማሳረፍ ችሏል፡፡ የስሎቬኒያን…

ዕቅድን በመፈጸም ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ እንደሚገባ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ዕቅዶችን ተግባራዊ በማድረግ የሕዝቡን የልማት ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ኡሞድ ኡጁሉ አሳሰቡ፡፡ ከ2013 እስከ 2015 በጀት ዓመት የተከናወኑ ተግባራትና የ2016 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ ተቋማት የተጠቃለለ…

ኔዘርላንድስ ፖላንድን 2 ለ 1 አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ17ኛው የ2024 የአውሮፓ ዋንጫ ጨዋታ ኔዘርላንድስ (ሆላንድ) ተጋጣሚዋን ፖላንድን 2 ለ 1 አሸንፋለች፡፡ ቡክሳ በ16ኛው ደቂቃ ባስቆጠራት ጎል ፖላንድ ተጋጣሚዋን ስትመራ ብትቆይም÷ ጋክፖ በ29ኛው ደቂቃ ኔዘርላንድስን አቻ ማድረግ ችሏል፡፡…

ወላይታ ድቻ ከመመራት ተነስቶ ሀድያ ሆሳዕናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ27ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወላይታ ድቻ ከመመራት ተነስቶ ሀድያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 ማሸነፍ ችሏል፡፡ ሀድያ ሆሳዕና በመጀመሪያው አጋማሽ በተመስገን ብርሃኑ ብቸኛ ጎል 1 ለ 0 እየመራ ወደ መልበሻ ክፍል አምርቷል፡፡ ከዕረፍት መልስ…

በ2024 የአውሮፓ ዋንጫ ዛሬ 3 ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2024 የአውሮፓ ዋንጫ መርሐ-ግብር ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡ በዚህም ቀን 10 ሠዓት ላይ በምድብ አራት የተደለደሉት ፖላንድ እና ኔዘርላንድስ (ሆላንድ) ይጫወታሉ፡፡ እንዲሁም ምሽት 1 ሠዓት በምድብ ሦስት የሚገኙት ስሎቬኒያ ከዴንማርክ…

የግብርናውን ዘርፍ ስኬት ለማስቀጠል ያለሙ ማሻሻያዎች ተደርገዋል- ሚኒስቴሩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በግብርናው ዘርፍ የመጣውን ተጨባጭ ለውጥ ለማስቀጠል በፋይናንስ አቅርቦት ላይ ማሻሻያ መደረጉን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት ተግዳሮቶችና ቀጣይ የመፍትሔ አቅጣጫዎች ላይ ያተኮረ የፌዴራል እና የክልል የሥራ ኃላፊዎች…