Fana: At a Speed of Life!

ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ከዓለም አቀፍ የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴ ከዓለም አቀፍ የቀይ መስቀልና ቀይ ጨረቃ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት ኬት ፎርብስ ጋር ተወያዩ፡፡ በውይይታቸውም÷ በአስቸኳይ የሰብዓዊ ዕርዳታ ላይ መምከራቸውን የፕሬዚዳንት ጽ/ቤት መረጃ አመላክቷል፡፡

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ መሬት ወስደው ሥራ ባልጀመሩ አልሚዎች ላይ እርምጃ እወስዳለሁ አለ

አዲስ አበባ፣መጋቢት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በምርጥ ዘር ብዜት ላይ ለመሰማራት መሬት ወስደው ሥራ ባልጀመሩ አልሚዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ግብርና ቢሮ አስታወቀ፡፡ የምርጥ ዘር ብዜት ሥራ ለማከናወን ስድስት ባለሃብቶች መሬት መውሰዳቸውን እና ሦስቱ ወደ ሥራ…

የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባላት በመዲናዋ እየተሠሩ ያሉ የልማት ኮሪደር ሥራዎችን እየጎበኙ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር እየተሠሩ የሚገኙ የከተማ እድሳትና የልማት ኮሪደር ሥራዎችን እየጎበኙ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤም ለምክር ቤቱ አባላት ገለጻ እያደረጉ ነው፡፡…

የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያረጋግጡ ናቸው – ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት የለውጥ ዓመታት የተመዘገቡ ስኬቶች የኢትዮጵያን ብልጽግና አይቀሬነት የሚያረጋግጡ መሆናቸውን በብልጽግና ፓርቲ የፌዴራል ተቋማት አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዓለሙ ስሜ (ዶ/ር) ገለጹ። የፌዴራል ተቋማት የብልጽግና ፓርቲ አባላት ማጠቃለያ…

የጋራ ትርክትን ለመገንባት የህዳሴ ግድብ የስኬት ምንጮችን መጠቀም እንደሚገባ ተመላከተ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀገርን በፅኑ መሰረት በማኖር የጋራ ትርክት ለመገንባት በሚደረገው ጥረት የታላቁ ህዳሴ ግድብን የስኬት ምንጮች በማሳያነት መጠቀም እንደሚገባ ርዕሳነ-መሥተዳደሮች አመላከቱ፡፡ በግድቡ ላይ የታየውን አንድነት ሌሎች ችግሮችን ለመቅረፍ እየተሠራ ባለው…

በመዲናዋ በ3 ዓመታት 12 ሺህ ትናንሽ የልጆች መጫወቻዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያዎች ለመገንባት እየተሠራ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሦስት ዓመታት 12 ሺህ ትናንሽ የልጆች መጫወቻዎች እና የስፖርት ማዘውተሪያዎችን ለመገንባት እየተሠራ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ አሥተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገለፁ። ከንቲባዋ በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ የሚገኘውን የብስራተ ገብርኤል…

የፌዴራል ተቋማት የብልጽግና ፓርቲ አባላት ማጠቃለያ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 21፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፌዴራል ተቋማት የብልጽግና ፓርቲ አባላት ማጠቃለያ ኮንፈረንስ "ቃልን በተግባር ለኢትዮጵያ ብልፅግና" በሚል መሪ ሐሳብ በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው። በኮንፈረንሱ ላይ÷ የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዚዳንት እና የዋና ጽ/ቤት ኃላፊ አደም ፋራህ፣…

በጋምቤላ ክልል አንድነትን ለማሻከር የሚሠሩትን በማጋለጥ ሕብረተሰቡ ትብብሩን እንዲያጠናክር ተጠየቀ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጋምቤላ ክልል የሕዝብን አንድነት ለማሻከር የሚሠሩ ጽንፈኛ ኃይሎችን አጋልጦ ለመንግሥት በመስጠት ረገድ ሕብረተሰቡ ትብብሩን እንዲያጠናክር የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ። የኮሚሽኑ ወንጀል መከላከል ዘርፍ ኃላፊ ምክትል ኮሚሽነር ጄኔራል…

50 የእጅ ቦምብ ለሸኔ የሽብር ቡድን ሊያቀብሉ ነበር ተብለው የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች ጥፋተኛ ተባሉ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 50 የእጅ ቦምብ ለሸኔ የሽብር ቡድን ሊያቀብሉ ነበር ተብለው የተከሰሱ ሁለት ግለሰቦች ላይ የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ ህገመንግስታዊና በህገመንግስት ስርዓት ላይ የሚፈጸሙ የወንጀል ጉዳዮችን የሚመለከተው ችሎት የጥፋተኝነት ፍርድ ሰጠ።…

በደቡብ አፍሪካ የ45 ሰዎች ሕይወት ካለፈበት አደጋ የ8 ዓመት ልጅ በሕይወት ተገኘች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ አፍሪካ የ45 ሰዎችን ሕይወት ከቀጠፈው የተሽከርካሪ አደጋ የስምንት ዓመት ልጅ በሕይወት መገኘቷ ተሰምቷል፡፡ ከቦትስዋና ዋና ከተማ ጋቦሮኔ ወደ ሞሪያ ከተማ ሲጓዝ የነበረ አውቶቡስ ተገልብጦ የ45 ሰዎች ሕይወት ማለፉን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡…