Browsing Category
ስፓርት
ፋሲል ከነማ እና ሲዳማ ቡና አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ)በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ እና ሲዳማ ቡና 2 አቻ ተለያይተዋል፡፡
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አስራ ስምንተኛ ሳምንት ጨዋታ በድሬዳዋ ስታዲየም ተካሂዷል፡፡
ፋሲል ከነማ እና ሲዳማ ቡና ቀን 10 ሰዓት ላይ ባደረጉት ጨዋታ…
አትሌት ጀማል ይመር የራሱን ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ኮሪያ በተካሄደው የሴዑል ማራቶን አትሌት ጀማል ይመር የራሱን ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ አሸንፏል፡፡
አትሌት ጀማል ውድድሩን ያሸነፈው 2 ሰዓት ከ 6 ደቂቃ ከ8 ሰከንድ በመግባት ሲሆን÷ ይህም የግሉ ፈጣን ሠዓት ሆኖ ተመዝገቧል፡፡
በፕሪሚየር ሊጉ 18ኛ ሣምንት መርሐ-ግብር ዛሬ ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ2016 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 18ኛ ሣምንት መርሐ-ግብር ዛሬ በድሬዳዋ ስታዲየም ሁለት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
በዚሁ መሠረት 10:00 ሠዓት ላይ ፋሲል ከነማ ከሲዳማ ቡና የሚጫወቱ ይሆናል፡፡
እንዲሁም 1:00 ሠዓት ላይ ወላይታ ድቻ እና…
ከ15 ሺህ ሴቶች በላይ የተሳተፉበት የ5 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 8፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ15 ሺህ ሴቶች በላይ የተሳተፉበት 21ኛ ዙር ቅድሚያ ለሴቶች የአምስት ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በአዲስ አበባ ተካሂዷል፡፡
በውድድሩም ጉታኒ ሻንቆ 1ኛ፣ ብርነሽ ደሴ 2ኛ እና መቅደስ ሽመልስ 3ኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቅቀዋል፡፡
መነሻ እና…
በስፔን የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ዮሚፍ ቀጄልቻ አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በስፔን ላሬዶ ከተማ በተካሄደ የ10 ኪሎ ሜትር ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ዮሚፍ ቀጄልቻ አሸንፏል፡፡
አትሌት ዮሚፍ ርቀቱን 26 ደቂቃ ከ36 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ቀዳሚ የሆነው፡፡
የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ችቦ የማብራት ንቅናቄ በቢሾፍቱ ከተማ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የፓሪስ 2024 ኦሎምፒክ ችቦ የማብራት ንቅናቄ በኦሮሚያ ክልል ቢሾፍቱ ከተማ ተካሂዷል።
በመጪው ሐምሌ ወር የሚካሄደውን የፓሪስ ኦሎምፒክ ምክንያት በማድረግ ሀገራዊ የኦሎምፒክ ችቦ ማብራት ንቅናቄ መጀመሩ ይታወቃል።
በትግራይ ክልል መቀሌ…
በ13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የሚሳተፈው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑክ ጋና ገባ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የሚሳተፈው ከ90 በላይ ሰዎችን ያካተተው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ልዑካን ቡድን አባላት ጋና አክራ ገብተዋል።
ልዑኩ ከአጭር እስከ መካከለኛ ርቀት የሚወዳደሩ አትሌቶች እና የሴቶች የቅርጫት ኳስ ቡድንን ያካተተ ነው፡፡…
ቅዱስ ጊዮርጊስ ሻሸመኔ ከተማን 2 ለ 0 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 7፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሻሸመኔ ከተማን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የቅዱስ ጊዮርጊስን የማሸነፊያ ግቦች አማኑኤል ኤርቦ በ70ኛው እና 86ኛው ደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡
ውጤቱን ተከትሎም ቅዱስ…
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻልና ሐዋሳ ከተማ ድል ቀናቸው
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው 18ኛ ሳምንት በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መቻልና ሐዋሳ ከተማ ድል ቀናቸው።
ምሽት 1:00 ላይ በተካሄደው የመቻል እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጨዋታ መቻል ጨዋታው እንደተጀመረ ምንይሉ ወንድሙ በሶስተኛው እና አቤል ነጋሽ…
በመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ሜዳሊያዋን አገኘች
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በ13ኛው የመላው አፍሪካ ጨዋታዎች ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ሜዳሊያዋን አግኝታለች፡፡
ዛሬ በተደረገው ከ23 አመት በታች የነጠላ ወንዶች ብስክሌት ውድድር ኪያ ጀማል 2ኛ በመውጣት የብር ሜዳሊያ አግኝቷል።
ደቡብ አፍሪካ ውድድሩን…