Browsing Category
ስፓርት
በሴቶች 10 ሺህ ከ30 ደቂቃ በታች በማጠናቀቅ ኢትዮጵያ ታሪክ ሰራች
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ሚዛን ዓለም የ10 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር በአሸናፊነት አጠናቃለች፡፡
አትሌቷ በለንደን ’’ኮንቲነንታል ቱር’’ ላይ በተደረገው የ10 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር ከ30 ደቂቃ በታች በመግባት በታሪክ 12ኛዋ እንስት ሆናለች፡፡…
አትሌት ጸሃይ ገመቹ በሕንድ ባንጋሉር የ10 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ጸሃይ ገመቹ በህንድ ባንጋሉር በተካሄደ የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸነፈች፡፡
አትሌት ጸሃይ ርቀቱን 31 ደቂቃ ከ38 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ነው በቀዳሚነት ያጠናቀቀችው፡፡
ከተማ አቀፍ የማርሻል አርት ስፖርታዊ ፌስቲቫል ተካሄደ
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ15ሺህ በላይ ስፖርተኞች የተሳተፉበት የማርሻል አርት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ ተካሂዷል።
መርሐ ግብሩ “የማርሻል አርት ስፖርት ለከተማችን ሰላም እና ውጤታማ ትውልድ ግንባታ” በሚል መሪ ቃል…
ሀምበሪቾ ዱራሜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 12 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀምበሪቾ ዱራሜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ።
2006 ዓ.ም የተመሰረተው ሀምበሪቾ ዱራሜ ከአራት ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግን ተቀላቅሎ ሲሳተፍ መቆየቱን ሶከር ኢትዮጵያ አስነብቧል።
ያለፉትን ዓመታት በሊጉ…
አቶ ውብሸት ደሳለኝ የብሄራዊ ቡድኑ የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)አቶ ውብሸት ደሳለኝ የዋሊያዎቹ የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ በመሆን መሾማቸውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡
ፌዴሬሽኑ በቀጣይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን በጊዜያዊነት እንዲመሩ ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማርያም እና አሰልጣኝ ደግአረገ…
የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጥሏል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤትኪንግ ኢትዮጵያን ፕሪሚየር ሊግ የደረጃ ሰንጠረዥ እየመራ የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ በሀዋሳ ከተማ ነጥብ ጥሏል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተደረገው የ24ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከእረፍት መልስ በቸርነት ጉግሳ…
ከ25ኛ ሳምንት በኋላ ያሉ ጨዋታዎች የዲ ኤስ ቲቪ ቀጥታ ስርጭት ሽፋን አያገኙም – ሊግ ኩባንያው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ25ኛ ሳምንት በኋላ ያሉ ጨዋታዎች የዲ ኤስ ቲቪ ቀጥታ ስርጭት ሽፋን እንደማያገኙ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ አክሲዮን ማህበር አስታወቀ፡፡
ማህበሩ በማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳስታወቀው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 ውድድር…
በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ ለገጣፎ ለገዳዲን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ ለገጣፎ ለገዳዲን አሸነፈ፡፡
በዛሬው እለት 9 ሰዓት ላይ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ለገጣፎ ለገዳዲን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የፋሲል ከነማ የማሸነፊያ…
የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በዛሬው እለት መጀመሩን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ገለጸ፡፡
52ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ሲጀመር በሴቶች ርዝመት ዝላይ፣ በወንዶች ከፍታ ዝላይ የፍጻሜ፣ እንዲሁም በ800 ሜትር ወንዶችና ሴቶች…
ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማርያም የዋልያዎቹ ጊዜያዊ አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 7፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማርያም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ጊዜያዊ አሰልጣኝ ሆነው መሾማቸውን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታውቋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድንን ላለፉት ሁለት ዓመታት ሲመሩ የቆዩት አሰልጣኝ ውበቱ አባተ በስምምነት ከብሄራዊ…