Fana: At a Speed of Life!
Browsing Category

ስፓርት

ብሄራዊ ቡድኑ ከሞዛምቢክ ጋር ለመጫዎት ዝግጁ ነው – አሰልጣኝ ውበቱ አባተ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ብሄራዊ ቡድኑ በነገው ዕለት ከሞዛምቢክ ጋር ለሚደርገው ጨዋታ ዝግጁ መሆኑን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ተናገሩ፡፡ በነገው ዕለት የሚካሄደውን ጨዋታ አስመልክቶ የብሔራዊ ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና አምበሉ መስኡድ መሐመድ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል።…

ዕለታዊ አጫጭር የውጭ ስፖርታዊ ዜናዎች

ቼልሲ ከ 17 ዓመት በኋላ በፕሪሚየር ሊጉ በፉልሃም 2 ለ 1 ተሸንፏል፤የትላንት ምሽቱን ውጤት ተከትሎም አሰልጣኝ ግራም ፖተርስ አጣብቂኝ ውስጥ ገብተዋል፡፡ በጨዋታው የተሰለፈው አዲሱ ፈራሚ ዣኦ ፊሊክስ ለፕሪሚየር ሊጉ የመጀመሪያ ጨዋታውን ቢያደርግም ሜዳ ውስጥ በፈጸመው ጥፋት በ58ኛው ደቂቃ…

 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በቦስተን ማራቶን ይሳተፋሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በቦስተን ማራቶን በሁለቱም ጾታዎች እንደሚሳተፉ የውድድሩ አዘጋጆች አስታውቀዋል፡፡ በወንዶች ምድብ ሌሊሳ ዴሲሳ፣ሹራ ቂጣታ፣ አንዳምላክ በልሁ ፣ አንዱዓለም በላይ እንዲሁም ሂርጳሳ ነጋሳ በውድድሩ ይካፈላሉ፡፡ በሴቶቹ ደግሞ…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለቻን ውድድር አልጄሪያ ገብቷል

አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቻን ውድድር አስተናጋጅ በሆነችው አልጄርያ በሰላም ገብቷል፡፡   ብሄራዊ ቡድኑ አልጀርስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በአልጀርያ ባህላዊ ሙዚቃ የታጀበ አቀባበል ተደርጎለታል።   ዋልያዎቹ በቻን…

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አልጄሪያ አቀና

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአልጄሪያ አስተናጋጅነት በሚካሔደው ሰባተኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ሻምፒዮና (ቻን) የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አልጀሪያ አቀና፡፡ ውድድሩ ከነገ በስቲያ ይጀመራል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለውድድሩ በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ…

የሴቶች ፕሪሚየር ሊግና የሴቶች ከፍተኛ ሊግ 2ኛ ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ይፋ ሆነ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ፣ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ እና ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን እና የዝውውር ጊዜ ይፋ ተደርጓል።   በዚህ መሰረትም የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ እና ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለተኛ ዙር…

አሸናፊ በቀለ የፋሲል ከነማ አሰልጣኝ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸናፊ በቀለ የፋሲል ከነማ አሰልጣኝ በመሆን አፄዎቹን በይፋ ተረክበዋል፡፡ ፋሲል ከነማ በዘንድሮው የሊግ ውድድር ደካማ አቋም ያሳየ ሲሆን ፥ ባደረጋቸው 13 ጨዋታዎች 17 ነጥቦችን ብቻ በመሰብሰብ 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡ በዚህም ክለቡ…

ዋሊያዎቹ በአቋም መፈተሻ ጨዋታ በሞሮኮ አቻቸው 2 ለ 1 ተሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በሁለተኛ ዙር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ በሞሮኮ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል፡፡ የቻን ዝግጅቱን በሞሮኮ ካዛብላንካ በማድረግ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታውን በዛሬው ዕለት ከሞሮኮ አቻው ጋር…

ጋሬዝ ቤል ከእግር ኳስ ሕይወትራሱን አገለለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዌልሳዊው ኢንተርናሽናል ጋሬዝ ቤል ራሱን ከክለብና ከብሄራዊ ቡድን ማግለሉን አስታውቋል፡፡ ቤል በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ÷ “የምወደውን የእግር ኳስ ስፖርት የመጫወት ህልሜን በማሳካቴ እድለኛ ነኝ ፤ነገር ግን ከዚህ በላይ…

ሮቤርቶ ማርቲኔዝ የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኑ፡፡ ስፔናዊው አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ÷ በዓለም ዋንጫው የተሰናበቱትን አሰልጣኝ ፈርናንዶ ሳንቶስ በመተካት ነው በዛሬው ዕለት የፖርቹጋል ብሔራዊ…