Fana: At a Speed of Life!

 ኢትዮጵያ በአፍሪካ አህጉር የዓለም የጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈች ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በጤና ሚኒስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ የተመራ ልዑክ በአፍሪካ አህጉር የዓለም ጤና ድርጅት መድረክ ላይ እየተሳተፈ ነው። 74ኛው የአፍሪካ አህጉር የዓለም የጤና ድርጅት መድረክ የኮንጎ ብራዛቪል ፕሬዚዳንት ዴኒስ ሳሶ ንጉዌሶ በተገኙበት ዛሬ…

የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ተብለው በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች ፍ/ቤት ቀረቡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ተብለው በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ዛሬ ከሰዓት በኋላ በተጠርጣሪ ዮሃንስ ዳንኤል በርሄ…

በኮሪደር ልማት ሥራ የተመዘገበው ውጤት በተሻለ ፍጥነት ተጠናክሮ ይቀጥላል- አቶ ኦርዲን በድሪ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረሪ ክልል በኮሪደር ልማት ሥራ የተመዘገቡ ውጤቶች በተሻለ ፍጥነት ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ርብርብ እንደሚደረግ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪ ገለፁ። አቶ ኦርዲን በድሪ የሐረር ከተማን ስትራቴጂክ የልማት እቅድ ለመምራት ከተቋቋመው ግብረ…

ኢትዮጵያና ሞሮኮ ወታደራዊ ትብብራቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የጦር ሃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ከሞሮኮ ብሄራዊ መከላከያ አስተዳደር ተጠሪ አብዱላጢፍ ሉዲ ጋር ተወያይተዋል፡፡ በውይይታቸውም÷ ሀገራቱ ያላቸውን ወታደራዊ ትብብር ማጠናከር በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል፡፡…

በ2024 አጋማሽ የሩሲያ ኢኮኖሚ በ4 ነጥብ 6 በመቶ ማደጉ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን በፈረንጆቹ 2024 የመጀመሪያ አጋማሽ የሩሲያ ምጣኔ ሀብት (ጂዲፒ) በ4 ነጥብ 6 በመቶ ማደጉን አስታወቁ፡፡ ፕሬዚዳንቱ የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ሁኔታ አስመልክቶ ባደረጉት የቪዲዮ ኮንፈረንስ ላይ “እንዳለፈው ዓመት…

በሰሜን ጎንደር ዞን በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ23 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን በተከሰተ የመሬት መንሸራተት አደጋ የ23 ወገኖች ሕይወት ሲያልፍ ሥምንት ሰዎች የአካል ጉዳት ደረሰባቸው፡፡ አደጋው የተከሰተው በዞኑ በሚገኙ አራት ወረዳዎች በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች መሆኑን የዞኑ አደጋ…

የሰውሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ሚናን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት ለመገናኛ ብዙኃን አመራር እና ባለሞያዎች በሰውሰራሽ አስተውሎት እና የሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ወርቁ ጋቸና (ዶ/ር) በዚህ ወቅት÷ የሚዲያ…

የአየር ትራንስፖርት ዘርፉን ቀልጣፋና ደህንነቱ የተጠበቀ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአየር ትራንስፖርት ኢንዱስትሪውን አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋ፣ አስተማማኝ እና ደህንነቱ የተጠበቀ ለማድረግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ፡፡ የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ጌታቸው መንግስቴ እንዳሉት÷…

አቶ ጥላሁን ከበደ የሕዝብ ትስስርን በማጠናከር ክልሉን ማሳደግ እንደሚገባ አስገነዘቡ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) ጥላቻን በፍቅር፤ ጥርጣሬን በእምነት በመቀየር የሕዝብ ለሕዝብ ትስስርን በማጠናከር ክልሉን ማሳደግ እንደሚገባ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ፡፡ ርዕሰ መሥተዳድሩ "ከነሐሴ እስከ ነሐሴ" በሚል ርዕስ የክልሉን ምስረታ…

50 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት ወደሀገር ውስጥ እየተጓጓዘ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 20፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) 50 ሚሊየን ሊትር የምግብ ዘይት ከጅቡቲ ወደ ኢትዮጵያ እየተጓጓዘ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ከጅቡቲ ወደ ተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች እየተጓጓዘ ያለው የምግብ ዘይት የኑሮ ውድነትን ለማሻሻል እና ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል የገበያ ዋጋን ለማረጋጋት ታስቦ…