Fana: At a Speed of Life!

ሚኒስቴሩ የማዕድን ምዘናና የምርምር ላቦራቶሪ ለመገንባት ከኤስ ጂ ኤስ ግሩፕ ጋር ተፈራረመ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የማዕድን ሚኒስቴር የማዕድን ምዘናና የምርምር ላቦራቶሪ ለመገንባት ከኤስ ጂ ኤስ ግሩፕ ጋር ስምምነት ተፈራርሟል፡፡   ላቦራቶሪው በ2 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር ወጪ የሚገነባ መሆኑን የማዕድን ሚኒስትር ታከለ ኡማ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው…

የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም  ወንጀሎችን ከሚፈፅሙ ግለሰቦች ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ስልክ እየደወሉ እና የተለያዩ የማጭበርበር ዘዴዎችን በመጠቀም ወንጀሎችን ከሚፈፅሙ ግለሰቦች ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጥሪ አቀረበ ፡፡ በአዲስ አበባ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለያዩ ስልኮች በመደወል እንኳን ደስ አላችሁ ሎተሪ…

ጠ/ሚ ዐቢይ ትናንት የተከፈተውን ዓለም አቀፍ ማዕድንና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 2 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ትናንት የተከፈተውን ዓለም አቀፍ ማዕድንና ቴክኖሎጂ ኤክስፖ ጎበኙ። ኤክስፖው ትናንት ፕሬዚዳንት ሣኅለወርቅ ዘውዴን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በሚሊኒየም አዳራሽ መከፈቱ ይታወሳል፡፡…

የኮሙኒኬሽን ተቋማት የሠላም ስምምነቱን መንፈስ በመከተል መረጃዎችን ተደራሽ በሚያደርጉበት ሁኔታ ላይ ውይይት ተደረገ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 2 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ከክልል እና የከተማ መሥተዳደር የኮሙኒኬሽን ተቋማት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ጋር በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል፡፡ የውይይቱ ዓላማ የመንግስት ኮሙኒኬሽን ተቋማት የሠላም ስምምነቱ መርሆችንና…

አገልግሎቱ ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ከ1 ሺህ በላይ መጻሕፍትን አበረከተ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 2 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የስደተኞችና ተመላሾች አገልግሎት ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት ከአንድ ሺህ በላይ መጻሕፍትን አበርክቷል፡፡ መጻሕፍቶቹን የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ተስፋሁን ጎበዛይ ለአብርሆት ቤተ መጻሕፍት የበላይ ጠባቂ ኢንጅነር ውባየሁ ማሞ አስረክበዋል፡፡…

ጆ ባይደን ከ ሺ ጂንፒንግ ጋር ሊወያዩ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 2 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን ወደ መንበረ-ሥልጣን ከመጡ ወዲህ ከቻይናው አቻቸው ሺ ጂንፒንግ ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ ሊወያዩ መሆኑ ተገለጸ፡፡ ሁለቱ ወገኖች የሚገናኙት በቀጣዩ ሳምንት ኢንዶኔዢያ ላይ በሚካሄደው የቡድን 20 አባል ሀገራት ጉባዔ…

ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚያስፈልጉ የግብርና ምርቶች ዋጋ ላይ ያተኮረ ውይይት እየተካሔደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለአምራች ኢንዱስትሪው የሚያስፈልጉ የግብርና ምርቶች ጥራት ፣መጠን እና ዋጋ ላይ ያተኮረ የምክክር መድረክ እየተካሔደ ነው፡፡ የአምራች ኢንዱስትሪ ዘርፉ የሚጠበቅበትን እንዲያሳካ የግብዓት አቅርቦት እጥረት እና የጥራት ችግሮችን በመለየት ባለድርሻ…

የሶማሌ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ላይ እየተወያዩ ነው

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ከፍተኛ የሥራ ሀላፊዎች በወቅታዊ ሃገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት ማካሄድ ጀምረዋል። በውይይቱ ላይ የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ዑስማን፣ የብልፅግና ፓርቲ የሶማሌ ክልል ፅህፈት ቤት ሀላፊ መሀመድ ሻሌና የክልሉ…

የመዲናዋ የወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ የታገዱ አገልግሎቶችን ከመጀመሩ በፊት በሕትመቶች ላይ ለውጥ ማድረጉን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የወሳኝ ኩነት ምዝገባ እና መረጃ ኤጀንሲ የታገዱ አገልግሎቶችን ከመጀመሩ አስቀድሞ በሁሉም ሕትመቶች ላይ የሕትመት ለውጥ ማድረጉን አስታውቋል።   የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ዮናስ ዓለማየሁ እንደገለጹት÷…

የጤና ባለሙያዎችን በጥናት በተደገፉ አሰራሮች ማገዝ ለዘርፉ ውጤታማነት ፋይዳው የጎላ ነው-ዶ/ር ሊያ ታደሰ

አዲስ አበባ፣ ሕዳ ር 2፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጥናት የተደገፉ አሰራሮችን በመዘርጋት ለጤና ባለሙያዎች ድጋፍ ማድረግ ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ የሚኖረው ፋይዳ የጎላ ነው ሲሉ የጤና ሚኒስተር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለጹ፡፡ የጤናው ዘርፍ የሰው ሃብት ልማት፣ ብቃትና አስተዳደርን በጥናት በተደገፈ…