Fana: At a Speed of Life!

በሶማሊያ የመረጃና ደኅንነት ኤጀንሲ ኃላፊ የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገባ

አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 30 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሶማሊያ ብሔራዊ መረጃና ደኅንነት ኤጀንሲ ዳይሬክተር ጀነራል ማሀድ ሞሐመድ የተመራ ልዑክ አዲስ አበባ መግባቱን የብሔራዊ መረጃና ደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል። ልዑኩ ለሁለት ቀናት የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን…

ኮሚሽኑ በአማራና ትግራይ ክልሎች ከ342 ሚሊየን ብር በላይ የሰብዓዊ ድጋፍ ማድረጉን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራና ትግራይ ክልሎች ከጥቅምት 20 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ 342 ነጥብ 4 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጣ የሰብዓዊ ድጋፍ ማድረጉን የብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አስታውቋል፡፡ የኮሚሽኑ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደበበ ዘውዴ…

በኢትዮጵያ የፖላንድ ኤምባሲ ለአብርሆት ቤተ-መፃሕፍት የተለያዩ መፃሕፍትን አበረከተ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ የፖላንድ አምባሳደር ፕርዜምስታው ቦባክን ጨምሮ ሌሎች የኤምባሲው ተወካዮች በተገኙበት መፃሕፍቶችን ለአብርሆት ቤተ-መፃሕፍት ኃላፊ ኢንጂነር ውብአየሁ ማሞ አበርክተዋል። አምባሳደሩ ዛሬ ከተደረገው የመጻህፍት እገዛ ባለፈ በቀጣይ ተቋሙን…

በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው የነበሩ ከ140 ሺህ በላይ ወገኖች ወደቀያቸው መመለስ ጀመሩ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጦርነቱ ምክንያት ተፈናቅለው የነበሩ ከ140 ሺህ በላይ ወገኖች ወደ ቀደመ ቀያቸው መመለስ መጀመራቸውን የሰሜን ጎንደር ዞን አስታወቀ። የሰሜን ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ተጠሪ ጽሕፈት ቤት እንደገለጸው÷ በዞኑ ከተለያዩ ወረዳዎች…

በሐረሪ ክልል የ2015 በጀት ዓመት የበጋ መስኖ ልማት ሥራ በይፋ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሐረሪ ክልል ሁለተኛው ዙር የ2015 በጀት ዓመት የበጋ መስኖ ልማት ሥራ በይፋ ተጀምሯል። የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ሚስራ አብደላ እንደገለጹት÷ በክልሉ በ2015 በጀት ዓመት ከ4 ሺህ ሔክታር…

ሁለት የዕደ ጥበብ ምርቶች በዓለም አቀፍ ምድብ የንግድ ምልክት ተመዘገቡ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁለት የኢትዮጵያ የዕደ ጥበብ ምርቶች በዓለም አቀፍ ምድብ የንግድ ምልክት (ብራንድ) መመዝገባቸውን የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ በንግድ ምልክትነት የተመዘገቡት የዕደ ጥበብ ምርቶችም÷ የሐረር ጌይ ሞኦት (አለላ…

ከ2 ቢሊየን ብር በላይ ወጪ የተደረገበት የዓሊ ከተማ የአስፋልት መንገድ ግንባታ ተጠናቀቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓሊ ከተማ የዋቤ ድልድይ ኮንክሪት አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁ ተገለጸ፡፡ 56 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የአስፋልት መንገድ ሙሉ በሙሉ መጠናቀቁን ተከትሎ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እየሰጠ እንደሚገኝ ከመንገዶች…

ኢትዮጵያና ሳዑዲ አረቢያ በንግድና ኢንቨስትመንት ዘርፍ አጋርነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ኢንቨስትመንት ኮሚሽነር ሌሊሴ ነሜ በኢትዮጵያ ከሳዑዲ አረቢያ አምባሳደር ፋሃድ አልሁማይዳኒ ጋር ተወያዩ። በውውይታቸው ወቅት በሀገራቱ ኢኮኖሚያዊ ትብብር ዙሪያ መምከራቸውን በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው አስታውቀዋል። በዚህ ወቅትም…

የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፖርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ለሰላም ስምምነቱ ተፈፃሚነት ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጠየቀ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ የፖለቲካ ፖርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሰላም ስምምነቱ በመርህ ደረጃ ተፈፃሚ እንዲሆን ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጠየቀ፡፡ ምክር ቤቱ ዛሬ በሰጠው መግለጫ በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል…

አሜሪካ እና ሩሲያ በይደር ያቆዩትን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ቅነሳ ድርድር ሊጀምሩ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ እና ሩሲያ የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ቅነሳ ላይ ለመምከር ሊገናኙ ነው። የአሜሪካ እና የሩሲያ ዲፕሎማቶች በቅርብ ጊዜ ውስጥ በግብፅ እንደሚገናኙ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኔድ ፕራይስ መናገራቸውን አር ቲ የአሜሪካ የዜና…