Fana: At a Speed of Life!

የ2013 በጀት አመት የሁሉም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች አፈጻጸም እየተገመገመ ነው

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የ2013 በጀት አመት የሁሉም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች አፈጻጸም እየተገመገመ ይገኛል። ሁሉም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች ሪፖርታቸውን አቅርበው ጠንካራ እና ደካማ ጎኖች እየተገመገሙ ነው። ግምገማው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት…

ህወሓት ህጻናትን በጦር ግንባር ማሰለፉ ለሰብአዊ መብቶች መከበር ደንታ እንደሌለው ማሳያ ነው – የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የህወሓት ቡድን ህጻናትን በጦር ግንባር ማሰለፉ ለሰብአዊ መብቶች መከበር ደንታ እንደሌለው ማሳያ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡…

በአማራ ክልል በአንድ ጀምበር የ247 ሚሊየን ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል የ2013 የአረንጓዴ አሻራ በአንድ ጀምበር የ247 ሚሊየን ችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር እየተካሄደ ይገኛል። በዛሬው ዕለትም 247 ነጥብ 8 ሚሊየን ችግኞች በ24 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ይተከላሉ ተብሏል። በክልሉ ርዕሰ መዲና…

በአዲስ አበባ የተካሔደው የድጋፍ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ የተካሔደው የድጋፍ ሰልፍ በሰላም መጠናቀቁን የአዲስ አበባ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች አሸባሪው የህወሓት ጁንታ ኢትዮጵያን ለማፈራረስ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ…

ውጊያ ለመክፈት ተደጋጋሚ ሙከራ ያደረገው የአሸባሪው ትህነግ ቡድን ሰብዓዊ ኪሳራ እየደረሰበት መሆኑን የምኒልክ ብርጌድ አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸባሪው ትህነግ ቡድን በወልቃይት ማይጋባ በሚገኘው የተከዜ ድልድይ አካባቢ ጥቃት ለመፈጸም ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርግም በአማራ ልዩ ኀይል ርምጃ እየተወሰደበት ነው። የፌዴራል መንግሥት የተናጠል ሰብዓዊ የተኩስ አቁም ውሳኔ ማሳለፉን ተከትሎ…

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት 12ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ነው

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክርቤት የ5ኛ ዓመት 6ኛ የሥራ ዘመን 12ኛ መደበኛ ጉባኤውን ዛሬ ማካሄድ ጀመረ፡፡ ምክር ቤቱ በክልሉም ሆነ በሃገራችን በተፈጠሩ የተለያዩ የጸጥታ ችግሮች ለደረሰው የሰው ሕይወት መጥፋትና መፈናቀል የሕሊና ጸሎት…

አሸባሪው ህወሃት የትግራይም ሆነ የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ጠላት ነው – የአዲስ አበባ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ህወሃት የትግራይም ሆነ የመላው ኢትዮጵያውያን የጋራ ጠላት ነው ሲሉ የአዲስ አበባ ሴቶች ማህበር ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ሁሉሃገርሽ ታዘዘ ገለጹ፡፡ የህወሃት ሽብር ቡድንን በመቃወም የሃገር መከላከያ ሰራዊትን የሚደግፍ ሰላማዊ ሰልፍ የአዲስ አበባ ሴቶችና…

ለየትኛውም ምድራዊ ሀይል በፍቅር እንጂ በሓይል የማይንበረከከው ህዝባችንን ይዘን የሚያጋጥሙን ፈተናዎችን ሁሉ በድል ስለምንሻገር ነው –

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የህወሓት ጁንታን የሚቃወምና የሀገር መከላከያ ሠራዊትን የሚደግፍ ሰላማዊ ሰልፍ በመስቀል አደባባይ ተካሂዷል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ተገኝተው ንግግር አድርገዋል። በዚህ…

የህዳሴው ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት ለቀጠናው እድገትና ትብብር መለያ ነው – ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የህዳሴው ግድብ ሁለተኛ ዙር የውሃ ሙሌት በአካባቢው ችግር ካለመፍጠሩ ባሻገር ለቀጠናው እድገትና ትብብር መለያ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለፁ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በትዊተር ገፃቸው በአረብኛ ቋንቋ…

ጁንታው በሑመራ ከተማ የማይካድራ ዓይነት ጭፍጨፋ ለመፈጸም ያሰበው ዕቅድ ተጋልጧል – የመረጃ ማጣሪያ

አዲስ አበባ ፣ ሐምሌ 15 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የህወሃት ጁንታ የማይካድራ ዓይነት ጭፍጨፋ በሑመራ ከተማ ለመፈጸም ያሰበው ዕቅድ ማፈትለኩን የወቅታዊ ሁኔታ የመረጃ ማጣሪያ አስታወቀ፡፡ በዕቅዱ መሠረት ከትግራይ ክልልና ከሱዳን አስርጎ በሚያስገባቸው ሠርጎ ገቦች አማካኝነት…