Fana: At a Speed of Life!

አትሌት ሻለቃ ሃይሌ ገብረስላሴ በጉራጌ ዞን በኢንቨስትመንት ለመሰማራት ቦታ ተረከበ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ሻለቃ ሃይሌ ገብረስላሴ በጉራጌ ዞን ወልቂጤ ከተማ አስተዳደር በሆቴል ኢንቨስትመንት ለመሰማራት 5 ሺህ 352 ካሬ ሜትር ቦታ መረከቡ ተገለፀ፡፡ በዞኑ በኢንቨስትመንት ለሚሰማሩ አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደረግም ተገልጿል።…

በትግራይ ክልል እየተደረገ ከሚገኘው ድጋፍ 70 በመቶው በመንግስት የተሸፈነ መሆኑ ተገለጸ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በትግራይ ክልል እየተደረገ ከሚገኘው ድጋፍ 70 በመቶው በመንግስት የተሸፈነ ሲሆን ቀሪው የአጋር አካላት ድርሻ መሆኑንብሔራዊ የአደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገለጸ። በትግራይ ክልል ለ4 ነጥብ 1 ሚሊየን ሕዝብ በመንግስትና በአጋር አካላት…

በኢትዮጵያ 2 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት በወራሪ መጤ እፅዋት ዝርያዎች መያዙ ተገለጸ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ 2 ነጥብ 1 ሚሊየን ሄክታር መሬት በወራሪ መጤ እፅዋት ዝርያዎች መያዙን የአካባቢ፣ ደንና አየር ንብረት ለውጥ ኮሚሽን ገለፀ፡፡ በተጨማሪም እስካሁን 35 ያህል የሚሆኑ የወራሪ መጤ ዝርያዎች መለየታቸውን ገልጿል። በመሆኑም…

በ6ኛው አጠቃላይ ምርጫ ከ134 ሺህ በላይ የአገር ውስጥ ታዛቢዎች ይሰማራሉ ተብሎ ይጠበቃል -ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛዉን አጠቃላይ ምርጫ ለመታዘብ ለሲቪል ማህበራት እውቅና የመስጠት ስራውን አጠናቀቀ። በዚህም በ6ኛው አጠቃላይ ምርጫ ከ134 ሺህ  109  የአገር ውስጥ ታዛቢዎች ይሰማራሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ቦርዱ ገልጿል።…

በሱዳን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን መንግስት በትግራይ ክልል የወሰደውን ህግ የማስከበር እርምጃ የሚደግፍ ሰልፍ አካሄዱ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሱዳን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልድ ኢትዮጵያውያን "ለሀገራችን  ሉዓላዊነትና አንድነት ከመንግስታችን ጎን እንቆማለን" በሚል መሪ ቃል ህዝባዊ የድጋፍ  ሰልፍ አደረጉ። በሺዎች የሚቆጠሩ በሱዳን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልድ…

በኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል  የተመራ ልዑክ ለስራ ጉብኝት ደቡብ ሱዳን ገባ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል እና ልዑካናቸው ለስራ ጉብኝት  ደቡብ ሱዳን ጁባ ገብቷል ። የልዑካን ቡድኑ ጁባ የገባው በደቡብ ሱዳኑ ብሔራዊ ፖሊስ አገልግሎት ሃላፊ ጄኔራል ማጃክ አከክ ግብዣ መሆኑ…

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ በአገሪቷ ላይ የተከፈተውን ያልተገባ ጫና ለመመከት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች በአገሪቷ ላይ የተከፈተውን ተገቢ ያልሆነ ጫና ለመመከት ጥረት እያደረጉ መሆኑን የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ኤጀንሲ ገለጸ። መንግስት በትግራይ ክልል ከወሰደው የሕግ ማስከበር እርምጃ…

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በመደበኛ ፖሊስ ሳይንስ ስልጠና ያሰለጠናቸውን 3 ሺህ 100 ፖሊሶችን አስመረቀ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በመደበኛ ፖሊስ ሳይንስ ስልጠና ያሰለጠናቸውን 3 ሺህ 100 ፖሊሶችን አስመርቋል፡፡ ፖሊሶቹ ለአምስት ወራት በአካል ብቃት፣ በቴኳንዶ፣ በአድማ ብተና እንዲሁም በወታደራዊ ሰልፍና በወንጀል ምርመራ የሰለጠኑ ሲሆን፥…

21 የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱን የኦሮሚያ ፖሊስ ገለጸ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት ሁለት ሳምንታት በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች በተደረገ የሕግ የበላይነት የማስከበር ስራ 21 የኦነግ ሸኔ አባላት ላይ እርምጃ መወሰዱንና 96 ግብረ አበሮቻቸው በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል፡፡ የኦሮሚያ…