Fana: At a Speed of Life!

በአማራ ክልል በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ በትራፊክ አደጋ የ30 ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል በምስራቅ ጎጃም አስተዳደር ዞን በሁለት እጁ እነሴ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 30 ሰዎች ለህልፈት ተዳረጉ፡፡ አደጋው በወረዳው በቤዛ ብዙሃን ቀበሌ ልዩ ስሙ ቡሃች በተባለ ቦታ በዛሬው ዕለት ማለዳ 1 ሰዓት ላይ ነው የደረሰው፡፡…

በትግራይ ክልል ከሚገኙ ሆስፒታሎች ውስጥ 75 በመቶዎቹ ሙሉ በሙሉ ስራ ጀመሩ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 6 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የብሄራዊ ድንገተኛ አደጋ አስተባባሪ ማዕከል በትግራይ ክልል ከሚገኙ ሆስፒታሎች ውስጥ 75 በመቶዎቹ ሙሉ በሙሉ ስራ መጀመራቸውን አስታወቀ፡፡ በአባል ሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች የተከናወኑ የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ እንዲሁም የመልሶ ማቋቋም…

አሜሪካ ከ100 ሚሊየን በላይ ዜጎቿን የኮቪድ19 ክትባት ሰጠች

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 6፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አሜሪካ ከ100 ሚሊየን በላይ ለሚሆኑ ዜጎቿ ቢያንስ አንድ ጊዜ የኮቪድ19 ክትባት መስጠቷን አስታወቀች፡፡ የፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አስተዳደር ክትባቱን በሀገር አቀፍ ደረጃ በስፋትና በፍጥነት ለማዳረስ እየጣረ ነው ተብሏል፡፡ ባይደንም…

ባለስልጣኑ ሉዓላዊነት እና አብሮነትን በሚፈታተኑ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ

አዲስ አበባ ፣ መጋቢት 6 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን  ሉዓላዊነት እና አብሮነትን የሚፈታተኑ ሚዲያዎች ላይ እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ። የባለስልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን አንዷለም ÷በትግራይ ክልል የተካሄደውን የህግ ማስከበር ዘመቻ ተከትሎ…

ሸሙ የምግብ ዘይት ፋብሪካ የማስፋፊያ ስራውን አጠናቆ በቀን 950 ቶን ዘይት ማምረት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በ1 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር የማስፋፊያ ስራ ሲከናወንለት የቆየው የሸሙ ሀላፊነቱ የተወሰነ የግል ድርጅት የምግብ ዘይት ፋብሪካ በቀን 950 ቶን ዘይት ማምረት ጀመረ። ድርጅቱ በድሬዳዋ ከተማ ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ የምግብ ዘይት ምርት የጀመረ ቢሆንም፤…

በድሬዳዋ ከተማ በከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮጀክት ታቅፈው የነበሩ አባወራዎች ተመረቁ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር በከተማ ልማታዊ ሴፍትኔት ፕሮጀክት ታቅፈው የነበሩ ከ3 ሺህ በላይ አባወራ ተጠቃሚዎች ተመረቁ። በከተማ ነዋሪዎች ላይ የሚስተዋለውን የምግብ ዋስት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ታስቦ በሃገር አቀፍ ደረጃ በመተግበር ላይ…

የዋና ስፖርት ዳኛ ኢንስፔክተር ሲሳይ ወየሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አንጋፋው የውሃ ዋና ስፖርት ዳኛ ኢንስፔክተር ሲሳይ ወየሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡ በኢትዮጵያ ውሃ ዋና ስፖርት ውስጥ በዳኝነትና በአሰልጣኝነት ለረጅም ጊዜ ያገለገሉት ኢንስፔክተር ሲሳይ ወየሳ ዛሬ በድንገት ሕይወታቸው ማለፉን የኢትዮጵያ ስፖርት…

በመጪው ክረምት ለሚካሄደው ሦስተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የችግኞች ዝግጅት እየተካሄደ ነው-ጠ/ሚ ዐቢይ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በመጪው ክረምት ለሚካሄደው ሦስተኛ ዙር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ ግብር የችግኞች ዝግጅት እየተካሄደ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ገለፁ። የግብርና ሚኒስቴር በ2013/14 የምርት ዘመን ለሚከናወነው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር በሀገር…

በሃላይደጌ ፓርክ በተከሰተ የእሳት አደጋ እስካሁን ከ100 ኪሎ ሜትር ስኩየር በላይ ሳርና ቁጥቋጦ ወደመ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በሃላይደጌ አሰቦት እጩ ብሄራዊ ፓርክ በተከሰተ የእሳት አደጋ እስካሁን ከ100 ኪሎ ሜትር ስኩየር በላይ የሚገመት ሳርና ቁጥቋጦ መውደሙን የፓርኩ አስተባባሪ አስታወቁ። ባለፈው ሀሙስ መጋቢት 2 ቀን 2013 ዓ.ም ቀትር ላይ በፓርኩ ሰሜናዊ ክፍል…

የሰው ሰራሽ የመተንፈሻ መሳሪያ እና የኦክስጅን እጥረት እያጋጠመ ስለሆነ ከመቼውም ጊዜ በላይ መጠንቀቅ ያስፈልጋል- ኢንስቲትዩቱ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከቀን ወደ ቀን በመላው ሀገሪቱ  በኮቪድ-19 ወረርሽኝ የመያዝ ምጣኔ ፤ ህይወታቸውን የሚያጡ እና የፅኑ ህክምና አገለግሎት የሚፈልጉ ታካሚዎች ቁጥር አስደንጋጭ በሆነ ሁኔታ እየጨመረ እንደሚገኝ የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢነስቲትዩት አስታወቀ።…