Fana: At a Speed of Life!

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎቻቸውን አስመረቁ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአሶሳ፣ መቅደላ ዓምባ እና የወቻሞ ዩኒቨርሲቲዎች በተለያዩ ትምህርት ዘርፎች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ተማሪዎችን ዛሬ አስመርቀዋል፡፡ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ከማል አብዱራሂም ዩኒቨርሲቲው 2 ሺህ 182 ተማሪዎችን ለ7ኛ…

በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር በደረሰ የትራፊክ አዳጋ የሁለት ሰዎች ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) በአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ፋግታ ለኮማ ወረዳ ትናንት በደረሰ የትራፊክ አዳጋ የሁለት ሰዎች ህይወት ሲያልፍ በሁለት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት መድረሱን የወረዳው ፖሊስ ጽህፈት ቤት አስታወቀ። በጽህፈት ቤቱ የመንገድ ደህንነትና…

የደቡብ ክልል የዚህ አመት የተፈጥሮና አካባቢ ጥበቃ የህብረተሰብ ተሳትፎ ንቅናቄ ጥር 18 ይጀመራል

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል የዚህ አመት የተፈጥሮና አካባቢ ጥበቃ የህብረተሰብ ተሳትፎ ንቅናቄ ከጥር 18 ቀን 2013ዓ.ም ጀምሮ ባሉት 30 ቀናት እንደሚካሄድ የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ አስታውቋል። ለዚህም ከ 5 ነጥብ 2 ሚሊየን በላይ…

ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የታቦት ማደሪያ ስፍራ አፀዱ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የሚገኝ የታቦት ማደሪያን ከተለያዩ እምነት ተከታይ አባቶችና ምእመናን ጋር በመሆን ፅዳት አከናውነዋል። ምክትል ከንቲባዋ ፅዳቱን ዮሴፍ…

የሚኒስትሮች ኮሚቴ የዕለት ደራሽ ድጋፍን ከማሳለጥ በተጨማሪ የተፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ የማቋቋምና መሰረተ ልማትን ወደነበረበት የመመለስ ርብርብ መቀጠሉን ገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የብሄራዊ አስቸኳይ ጊዜ አስተባባሪ ማዕከል ዘርፈ ብዙ ምላሽ ሰጪ የሚኒስትሮች ኮሚቴ የዕለት ደራሽ ድጋፍን ከማሳለጥ በተጨማሪ በየአካባቢው የተፈናቀሉ ወገኖችን መልሶ የማቋቋምና መሰረተ ልማትን ወደነበረበት የመመለስ ርብርብ መቀጠሉን ገለጸ።…

አቶ እርስቱ ይርዳው በጉራጌ ዞን እየተገነባ ያለውን የከሬብ መካለኛ መስኖ ፕሮጀክት ግንባታ ሂደትን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የደቡብ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ እርስቱ ይርዳው በጉራጌ ዞን በሙሁር አክሊል ወረዳ ከ260 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ ያለውን የከሬብ መካለኛ መስኖ ፕሮጀክት የግንባታ ሂደትን ጎብኝተዋል፡፡ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ…

4ኛው ከተማ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ ጥር 9፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ወይዘሮ አዳነች አቤቤ ለሀገሬ ሰላም ዘብ እቆማለሁ፤ ለመከላከያ ሰራዊት ቅድሚያ እሰጣለሁ በሚል መሪ ቃል 4ኛው የማሰ ስፖርት ላይ ተሳትፈዋል። በዚህም ወቅት ምክትል ከንቲባዋ…

የአነስተኛና መካከለኛ ማምረቻ ኢንዱስትሪ ልማትን በማስፋፋት ፍትሃዊ፤ ዘለቄታዊና ተስማሚ የስራ እድል መፍጠር እንደሚገባ ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) የአነስተኛና መካከለኛ ማምረቻ ኢንዱስትሪ ልማትን በማስፋፋትና መዋቅራዊ ሽግግሩን በማፋጠን ፍትሃዊ፤ ዘለቄታዊና ተስማሚ የስራ እድል መፍጠር እንደሚገባ ተገለጸ፡፡ የፌዴራል የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አዘጋጅነት በአነስተኛና መካከለኛ ማንፋክቸሪንግ…

ተጨማሪ 446 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተገለጸ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ 6 ሺህ 111 የላቦራቶሪ ናሙና ምርመራ 446 ሰዎች በኮሮና ቫይረስ መያዛቸው ተረጋግጧል። በኢትዮጵያ በአጠቃላይ እስካሁን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 130 ሺህ 772 ደርሷል። በሌላ በኩል 617 ሰዎች…

ጁንታው የኦሮሞ ወጣቶችን፣ ምሁራንና ታዋቂ ግለሰቦችን ጭምር የበላ ነው – አቶ ሽመልስ አብዲሳ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ) ለኢትዮጵያ ሁለንታናዊ ግንባታ ክልሉ ከፌዴራል መንግስት ጋር ተቀናጅቶ በትብብር እንደሚሰራ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ ገለጹ። ጁንታው የተሰጠውን ይቅርታ ወደ ጎን በመተው በንቀት ወደ ክህደት በመግባቱ ራሱን በራሱ በልቷል…