Fana: At a Speed of Life!

በፕሪሚየር ሊጉ ባህርዳር ከነማ ሲዳማ ቡናን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባህር ዳር ከነማ ሲዳማ ቡናን 3 ለ 1 አሸንፏል። የባህርዳር ከነማን ሁለት ግቦች ፍፁም አለሙ በ5ኛ እና 18ኛ ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር ሶስተኛውን ግብ በ53ኛው ደቂቃ ላይ ባየ ገዛኸኝ አስቆጥሯል።…

የኢትዮጵያ ገለልተኛ የብሄራዊ የኢኮኖሚ ምክር ቤት ተመሰረተ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ገለልተኛ የብሄራዊ የኢኮኖሚ ምክር ቤት መመስረቱን  የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት አስታውቋል። የመንግሥትን የማሻሻያ ፕሮግራም በስኬት ለማስፈጸምና በአጠቃላይ የኢኮኖሚውን እድገት ቀጣይነት ለማረጋገጥ የምሁራንና የባለሙያዎችን ምክር…

ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ከፈረንሳዩ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ከፈረንሳይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዦ ኢቭ ለድሮዮ ጋር ተወያይተዋል፡፡ ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዛሬ ማለዳ ላይ በኮትዲቯሩ ፕሬዚዳንት አላሳኔ ኦታራ በአለ ሲመት ላይ ለመገኘት ወደ ስፍራው ማቅናታቸው ይታወሳል፡፡…

የሴት ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ እንደ ሀገር ዝቅተኛ መሆኑ ተገለፀ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሴት ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ እንደ ሀገር ዝቅተኛ መሆኑን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ የትምህርት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ነቢል መህዲ በአሁኑ ጊዜ የሴት ተማሪዎች የትምህርት ተሳትፎ እንደ ሀገር ዝቅተኛ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ ሴት…

ተቋርጦ የነበረው የዩ ቲዩብ አግልግሎት ጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ተቋርጦ የነበረው ዩቲዩብን ጨምሮ የጎግል መተግበሪያዎች አገልግሎት ዳግም ጀመረ፡፡ ከዩቲዩብ በተጨማሪ የመልዕክት መላላኪያው ጂሜይል፣ ጎግል ድራይቭ እና ዶክስም ከበይነመረብ ላይ አገልግሎታቸው ተቋርጦ ነበር፡፡ በዓለም ዙሪያ የሚገኙ ተጠቃሚዎች…

የትግራይ ክልል የአየር መሥመር ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል- ባለስልጣኑ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የትግራይ ክልል የአየር መሥመር ለአገልግሎት ክፍት መሆኑን የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን አስታወቀ። በሰሜን ኢትዮጵያ ትግራይ ክልል የህግ ማስከበር ሂደትን ተከትሎ ተዘግቶ የነበረው የአየር ክልል ከዛሬ ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ በሰሜን…

በትግራይ ክልል የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ሙሉ ለሙሉ ወደነበረበት ለመመለስ እየተሰራ ነው

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) በትግራይ ክልል ተቋርጦ የነበረውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ሙሉ ለሙሉ ወደነበረበት ለመመለስ እየተሰራ መሆኑ ተገለጸ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን የመካከለኛና የዝቅተኛ የኤሌክትሪክ…

የቀድሞው የሊቨርፑል አሰልጣኝ ጄራርድ ሁዬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የቀድሞው የሊቨርፑል አሰልጣኝ ጄራርድ ሁዬ በ73 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ። ፈረንሳዊው አሰልጣኝ ጄራርድ ሁዬ ሊቨርፑልን ከፈረንጆቹ 1998 እስከ 2004 ድረስ በአሰልጣኝነት መርተውታል። በሊቨርፑል በነበራቸው ቆይታም የኤፍ ኤ ካፕ፣…

አፍሪካ በታዳሽ ሃይል ዘርፍ ያላትን አቅም መጠቀም ከቻለች የዜጎችን የሃይል ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ትችላለች – ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 5 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አፍሪካ በታዳሽ ሃይል ዘርፍ ያላትን እምቅ አቅም መጠቀም ከቻለች የዜጎችን የሃይል ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደምትችል የኢፌዴሪ የውሃ፣ መስኖና ኢነርጅ ሚኒስትር ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ ተናገሩ፡፡ ሚኒስትሩ በዓለም አቀፉ የውሃ አካላት…

በኢንስቲቲዩቱ የሚገኘው አላስፈላጊ የኬሚካል ክምችት መወገድ እንዳለበት ቋሚ ኮሚቴው አሳሰበ

አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 5፣ 2013 (ኤፍቢሲ) በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲቲዩት የሚገኘው አላስፈላጊ የኬሚካል ክምችት መወገድ እንዳበት በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና፣ አርብቶ አደርና አካባቢ ጥበቃ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ፡፡ ቋሚ ኮሚቴው ይህንን ያሳሰበው በምርምር ኢንስቲቲዩቱ…