Fana: At a Speed of Life!

የሀገር ክህደት ወንጀል በፈጸሙ ጀኔራል መኮንኖች፣ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችና የበታች ሹማምንቶች ላይ የመያዣ ትዕዛዝ ወጣባቸው

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሀገር ክህደት ወንጀል በፈጸሙ ጀኔራል መኮንኖች፣ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችና የበታች ሹማምንቶች ላይ የመያዣ ትዕዛዝ እንደወጣባቸው ተገለፀ፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት የላከው መግለጫ ቀጥሎ ይቀርባል፡፡…

ኢጋድ ቀጠናዊ ትስስር ለማምጣት ባለው ሚና ላይ ያተኮረ የዌቢናር ውይይት ተካሄደ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 9 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ቀጠናዊ ትስስርን ለማምጣት ባለው ሚና ላይ ያተኮረ የዌቢናር ውይይት ተካሄደ፡፡ ውይይቱን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከኢጋድ ሴክሬታሪያት ጋር በመተባባር ያዘጋጀው ነው ተብሏል፡፡…

ከፅንፈኛው ህወሃት እና ኦነግ ሸኔ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብው የተጠረጠሩ 287 ሰዎች ከጦር መሳሪያዎች ጋር በቁጥጥር ስር ውለዋል- ፌዴራል ፓሊስ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ባለፉት 14 ቀናት በተካሄደ ዘመቻ ከፅንፈኛው ህወሃት እና ኦነግ ሸኔ ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ 287 ሰዎች ከተለያዩ የጦር መሳሪያዎች ጋር በቁጥጥር ስር መወላቸውን የፌዴራል ፓሊስ አስታወቀ።…

በመዲናዋ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ከ118 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት ያላቸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ውል ተፈረመ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በ4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ከ118 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት ያላቸው የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶችን ለማከናወን ውል ተፈራረመ፡፡ ባለስልጣኑ ከ118 ኪ.ሜ በላይ ርዝመት ያላቸው የጋራ መኖሪያ…

የጋሞ ዞን ነዋሪዎች ለመከላከያ ሠራዊት 6 ሚሊየን ብር እና 77 ሠንጋዎችን ለሃገር መከላከያ ሰራዊት አበረከቱ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የደቡብ ክልል ጋሞ ዞን ነዋሪዎች ለሀገር መከላከያ ሠራዊት 6 ሚሊየን ብር እና 77 ሠንጋ በሬዎችን አበረከቱ፡፡ የጋሞ ዞን ዋና አስተዳዳሪ፣ የጋሞ ሀገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች የነዋሪዎቹን ድጋፍ ዛሬ በምድር ኃይል ግቢ ተገኝተው…

ባለስልጣኑ በአራት ወራት ውስጥ 245 ኪሎ ሜትር ልዩ ልዩ የመንገድ ጥገና ስራዎች አከናወነ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን በአራት ወራት ውስጥ 245 ኪሎ ሜትር ልዩ ልዩ የመንገድ ጥገና ስራዎችን ማከናወኑን አስታወቀ፡፡ ባለስልጣኑ ለትራፊክ እንቅስቃሴ አስቸጋሪ የሆኑ ዋና ዋና፣ የቀለበት መንገድ እንዲሁም የውስጥ ለውስጥ እና…

ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2 ሚሊየን ብር የማበረታቻ ሽልማት ተበረከተ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 9 ፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የ2 ሚሊየን ብር የማበረታቻ ሽልማት ተበረከተለት። ብሄራዊ ቡድኑ ትናንት የኒጀር አቻውን 3 ለ 0 ማሸነፋን ተከትሎ የኢፌዲሪ ስፖርት ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር በጋራ ሽልማቱን ማበርከታቸው ተገልጿል።…

ለሰራዊቱ እየተሰጠ ያለው ድጋፍና ክብር ዘመቻውን በፍጥነት ለመቋጨት ጉልበት ነው – የአየር ኃይል ምስራቅ ምድብ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍቢሲ) መላው ህዝብ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት እየሰጠ ያለው ድጋፍና ክብር የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እየተካሄደ ያለው ዘመቻ በፍጥነትና በስኬት እንዲጠናቀቅ አቅም የሚፈጥር መሆኑን የኢፌዴሪ አየር ኃይል የምስራቅ ምድብ ዋና አዛዥ ኮሎኔል አበበ ለገሰ አስታወቁ፡፡…

ማህበረሰቡ የአካባቢውን ሰላም ነቅቶ እንዲጠብቅ የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ

አዲስ አበባ ፣ ህዳር 9 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ማህበረሰቡ አካባቢውን ነቅቶ በመጠበቅና አጠራጣሪ ሁኔታዎችን ሲመለከት ጥቆማ በመስጠት ሊደርስ የሚችልን ጉዳት መከላከል እንደሚገባው የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪ አቀረበ፡፡ ለሰው ልጅ አስፈላጊ የሆነውን ሠላም ለመጠበቅ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ…

ም/ጠ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ህዳር 9፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሺሼኬዲ ጋር ተወያዩ። አቶ ደመቀ በነበራቸው ቆይታ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከፕሬዚዳንቱ ጋር ውይይት አድርገዋል።…