Fana: At a Speed of Life!

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የምግብ እጥረት እንዳያጋጥም ተጨማሪ 40 ሚሊዮን ኩንታል ሰብል ይመረታል- አቶ ዑመር ሁሴን

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 1፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ የምግብ እጥረት እንዳይፈጠር ከመኸር ምርት በተጨማሪ 40 ሚሊዮን ኩንታል ሰብል እንደሚመረት የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴን ገለጹ። 50 ሚሊዮን ኩንታል አትክልትና ፍራፍሬ ማምረት መጀመሩም ነው የተገለጸው።…

ከ40 ሚሊዮን ብር በላይ ግምት ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ በቁጥጥር ስር ዋለ

አዲስ አበባ፣ግንቦት 1፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) ባለፉት አምስት ቀናት የኮንትሮባንድ ዕቃዎችና በንግድ ማጭበርበር  ከ40 ነጥብ 3 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመቱ  ዕቃዎች በቁጥጥር ስር  መዋላቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ። ከሚያዝያ 26 እስከ 30 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ከተያዙት የገቢና ወጪ…

ሚኒስቴሩ የዘጠኝ ወር እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሄደ

አዲስ አበባ፣ግንቦት1፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ)የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር በዘርፍ የዘጠኝ ወር እቅድ አፈጻጸም ላይ ውይይት አካሂዷል። ሚኒስቴሩ ውይይቱን ከክልሎች እና ከሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ተጠሪ ተቋማት አመራሮች ጋር  በቪድዮ ኮንፍረስ  ያካሄደ ሲሆን÷በውይይቱም በእቅድ አፈጻጸም ወቅት…

የአውሮፕላን ነዳጅን ጨምሮ ሌሎች የነዳጅ ምርቶች ዋጋ ባለበት እንደሚቀጥል ተገለጸ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 1 ፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአውሮፕላን ነዳጅን ጨምሮ ሌሎች የነዳጅ የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ባለበት  እንዲቀጥል  መወሰኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታውቋል። መንግስት የሀገሪቱ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ በተረጋጋ ሁኔታ እንዲቀጥል ለማስቻል የአውሮፕላን…

የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ስነ- አዕምሮ ህክምና ክፍል ለኮቪድ-19 ህሙማን አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 1፣2012( ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል የስነ-አዕምሮ ህክምና ክፍል ለኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ህሙማን የህክምና አገልግሎት መስጠት ሊጀምር ነው። በሆስፒታሉ የስነ-አዕምሮ ህክምና ክፍል ሃላፊ ዶክተር አይዳ ከበደ ÷ሆስፒታሉ  የኮሮናቫይረስ ላለባቸው…

የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል ልማት የ10 ሚሊዮን ዶላር ብድር  ፈቀደ

አዲስ አበባ፣ግንቦት 1፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ)የአፍሪካ ልማት ባንክ ለኢትዮጵያ ታዳሽ ኃይል ልማት የ10 ሚሊዮን ዶላር ብድር   መፍቀዱን አስታወቀ። በረጅም ጊዜ የሚከፈለው ይህ ብድር  በቱሉ ሞዮ አካባቢ ለሚገነባው የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የሚውል መሆኑም ነው የተገለጸው። ፕሮጀክቱ…

በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ 16 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው የአንድ ሰው ህይወት አልፏል

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 2 ሺህ 383 የላብራቶሪ ምርመራ 16 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ቫይረሱ ተገኝቶባቸው በፅኑ ህክምና ላይ የነበሩ የ65 ዓመት ወንድ የአዲስ አበባ ነዋሪም ህይወታቸው…

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የግብርናና የትምህርት ሚኒስቴሮች ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ አደረጉ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የግብርና ሚኒስቴር እና የትምህርት ሚኒስቴር ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ድጋፍ አደረጉ። በሀገሪቱ የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽን ተከትሎ በቀረበው ጥሪ መሰረት በዛሬው ዕለት የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 2 ሚሊዮን…