Fana: At a Speed of Life!

ሀዋሳና ጎንደርን ጨምሮ ከተሞች የኮሮናቫይረስን ለመከላከል የተለያዩ ክልከላዎችንና ውሳኔዎችን እያሳለፉ ነው

አዲስ አበባ፣መጋቢት 24፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ሀዋሳ እና ጎንደርን ጨምሮ ሎሌች ከተሞች የኮሮናቫይረስ (ኮቪድ-19) ስርጭትን ለመከላከል የተለያዩ ክልከላዎችንና ውሳኔዎችን እያሳለፉ ነው። በሀዋሳ ከተማ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ስርጭት ለመከላከል ተጨማሪ ክልከላዎች መጣላቸውን የከተማዋ ምክትል…

አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከዴንማርክ የልማት ትብብር ሚኒስትር ራስመስ ፕረህን ጋር በስልክ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣መጋቢት 24፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ከዴንማርክ የልማት ትብብር ሚኒስትር ራስመስ ፕረህን ጋር በስልክ ተወያዩ። በነበራቸው ቆይታም ሁለቱ ሀገሮች በትብብር መስራት በሚቻሉባቸው የተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር…

የሀይማኖት ተቋማት በቤተ እምነቶች የሚደረጉ ሀይማኖታዊ ስርአቶች እንዲቆሙ በመወሰናቸው ኢ/ር ታከለ ምስጋና አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሀይማኖት ተቋማት የኮሮና ቫይረስን ለመከላከል ለሚደረገው ጥረት በቤተ እምነቶች የሚደረጉ ሀይማኖታዊ ስርአቶች እንዲቆሙ በመወሰናቸው እንዲሁም አዳራሽና ቦታቸውን መንግስት እንዲጠቀምበት በመፍቀድ ላሳዩት ቀና ተግባር ኢ/ር ታከለ ምስጋና አቀረቡ።…

በኢትዮጵያ ከኮሮናቫይረስ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 3 ደረሰ

አዲስ አበባ፣መጋቢት 24፣2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮሮናቫይረስ ከተያዙት ሰዎች መካከል አንድ ተጨማሪ ሰው ማገገሙን የጤና ሚኒስቴር ገለጸ። ከዚህ ቀደም ከህመሙ ማገገማቸው ከተገለጸው ሁለት ህሙማን በተጨማሪ ሌላ ሶስተኛ ሰው ማገገሙን ዶክተር ሊያ ታደሰ ተናግረዋል። ከዚም ባለፈ ባለፉት 24…

የገቢዎች ሚኒስቴር የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ከ14 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የገቢዎች ሚኒስቴር ከተጠሪ ተቋማት ጋር በጋራ በመሆን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ከ14 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ።   ድጋፉ የተደረገው በኢትዮጵያ የተከሰተውን የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል…

በማደግ ላይ ላሉ ሀገራት ድጋፍ እንዲደረግ ዶክተር ቴድሮስ ጥሪ አቀረቡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በማደግ ላይ ያሉ ሀገራትን እንዲደግፍ የአለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ጥሪ አቅርበዋል። የዓለም ጤና ድርጅት፣ የዓለም ባንክ እና ዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ወርርሽኙ በታዳጊ ሀገራት…

የጤና ባለሙያዎች ስለኮሮና የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጡ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 24፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ)የጤና ባለሙያዎች በተለያዩ የመዲናዋ ጎዳናዎች በመዘዋወር ኮሮናቫይረስ  ወረርሽኝን በተመለከተ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርት ሰጡ። የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቱን የሰጡት በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የልብ ህሙማንና ህፃናት መርጃ ማዕከል የሚገኙ…

በዓለም አቀፍ ደረጃ በጥቂት ቀናት ውስጥ በኮሮና ወረርሽኝ  የተያዙ ሰዎች ቁጥር ወደ 1 ሚሊዮን ከፍ ይላል-የአለም የጤና ድርጅት

አዲስ አበባ፣መጋቢት 24፣2012(ኤፍ.ቢ.ሲ) በአለም አቀፍ ደረጃ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ  የሚያዙ ሰዎች ቁጥር 1 ሚሊየን ይሆናሉ ሲል  የአለም የጤና ድርጅት አስታወቀ፡፡ ከዚያም ባለፈ  በቅርብ ቀናት ውስጥ በወረርሽኙ  ለህልፈት የሚዳረጉት ሰዎች ቁጥር ወደ 50…