ስፓርት
አትሌት ጸሃይ ገመቹ በሕንድ ባንጋሉር የ10 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር አሸነፈች
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ጸሃይ ገመቹ በህንድ ባንጋሉር በተካሄደ የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር አሸነፈች፡፡
አትሌት ጸሃይ ርቀቱን 31 ደቂቃ ከ38 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመግባት ነው በቀዳሚነት ያጠናቀቀችው፡፡
Read More...
ከተማ አቀፍ የማርሻል አርት ስፖርታዊ ፌስቲቫል ተካሄደ
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ15ሺህ በላይ ስፖርተኞች የተሳተፉበት የማርሻል አርት ፌስቲቫል በአዲስ አበባ በመስቀል አደባባይ ተካሂዷል።
መርሐ ግብሩ “የማርሻል አርት ስፖርት ለከተማችን ሰላም እና ውጤታማ ትውልድ ግንባታ” በሚል መሪ ቃል ነው የተካሄደው፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ወጣቶች ስፖርት…
ሀምበሪቾ ዱራሜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ
አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 12 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሀምበሪቾ ዱራሜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን አረጋገጠ።
2006 ዓ.ም የተመሰረተው ሀምበሪቾ ዱራሜ ከአራት ዓመታት በኋላ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግን ተቀላቅሎ ሲሳተፍ መቆየቱን ሶከር ኢትዮጵያ አስነብቧል።
ያለፉትን ዓመታት በሊጉ ሲሳተፍ ቆይቶ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ማደጉን…
አቶ ውብሸት ደሳለኝ የብሄራዊ ቡድኑ የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)አቶ ውብሸት ደሳለኝ የዋሊያዎቹ የግብ ጠባቂዎች አሰልጣኝ በመሆን መሾማቸውን የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡
ፌዴሬሽኑ በቀጣይ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድንን በጊዜያዊነት እንዲመሩ ኢንስትራክተር ዳንኤል ገብረማርያም እና አሰልጣኝ ደግአረገ ይግዛውን በዋና አሰልጣኝ እና ምክትል አልጣኝነት መሾሙ ይታወሳል፡፡
የግብ…
የሊጉ መሪ ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጥሏል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቤትኪንግ ኢትዮጵያን ፕሪሚየር ሊግ የደረጃ ሰንጠረዥ እየመራ የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ በሀዋሳ ከተማ ነጥብ ጥሏል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በተደረገው የ24ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከእረፍት መልስ በቸርነት ጉግሳ ጎል መምራት ቢችልም ተባረክ ሄፋሞ በፍፁም ቅጣት ምት ጎል አስቆጥሮ ሀዋሳን…
ከ25ኛ ሳምንት በኋላ ያሉ ጨዋታዎች የዲ ኤስ ቲቪ ቀጥታ ስርጭት ሽፋን አያገኙም – ሊግ ኩባንያው
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከ25ኛ ሳምንት በኋላ ያሉ ጨዋታዎች የዲ ኤስ ቲቪ ቀጥታ ስርጭት ሽፋን እንደማያገኙ የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ አክሲዮን ማህበር አስታወቀ፡፡
ማህበሩ በማህበራዊ ትስስር ገፁ እንዳስታወቀው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 ውድድር በሐዋሳ ከተማ እየተካሄደ መሆኑን እና ውድድሩ በቀጥታ የሱፐር ስፖርት ሽፋን እያገኘ…
በፕሪሚየር ሊጉ ፋሲል ከነማ ለገጣፎ ለገዳዲን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ፋሲል ከነማ ለገጣፎ ለገዳዲን አሸነፈ፡፡
በዛሬው እለት 9 ሰዓት ላይ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ለገጣፎ ለገዳዲን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የፋሲል ከነማ የማሸነፊያ ግቦችን የአማካይ ተጫዋቹ ሱራፌል ዳኛቸው በ45ኛው እና በ94ኛው ደቂቃ ላይ…