ስፓርት
ኪፕቾጌ በበርሊን ማራቶን ክበረ ወሰን በመስበር አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 15፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኬንያዊው ኢሉድ ኪፕቾጌ በበርሊን ማራቶን የራሱን ክበረ ወሰን በመስበር አሸንፏል፡፡
የዓለም አትሌቲክስ መረጃ እንደሚጠቁመው÷ አትሌቱ ዛሬ በተካሄደው የበርሊን ማራቶን 2:01:09 በሆነ ሰዓት በመግባት ነው ቀድሞ የነበረውን ሰዓት በ30 ሰኮንዶች በማሻሻል ክብረ ወሰኑን የሰበረው፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ …
Read More...
ወልቂጤ ከነማ የአማራ ባንክ ጣና ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነ
አዲስ አበባ፣መስከረም 14፣2015 (ኤፍ ቢሲ) ወልቂጤ ከነማ የ2015 የአማራ ባንክ ጣና ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኗል።
ክትፎዎቹ የዩጋንዳውን ክለብ ቡል ኤፍ ሲ 2 ለ 1 በማሸነፍ ነው ሻምፒዮን መሆን የቻሉት።
በባህርዳር ስታዲየም በተደረገው የፍፃሜ ጨዋታ ወልቂጤ ከመመራት ተነስቶ በሳሙኤል አስፈሪ እና ጌታነህ ከበደ ሁለት ጎሎች ማሸነፍ ችሏል።
የአማራ ባንክ ጣና ዋንጫ…
አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ የደልሂ ግማሽ ማራቶን አምባሳደር ሆነ
አዲስ አበባ ፣ መስከረም 13 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ኃይሌ ገብረሥላሴ በህንድ ዴልሂ በፈረንጆቹ ጥቅምት 16 የሚካሄደው ግማሽ ማራቶን ዓለም አቀፍ ዝግጅት አምባሳደር ሆኗል፡፡
የህንዱ የስፖርት መፅሄት የሆነው ዘ ሂንዱ እንዳስታወቀው የሁለት ጊዜ የኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳልያ አሸናፊው ኃይሌ ገብረሥላሴ በፈረንጆቹ ጥቅምት 16 ቀን በሚካሄደው የቬዳንታ ደልሂ ግማሽ…
ከ23 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድኑ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር አቻ ተለያየ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በአፍሪካ ከ23 ዓመት በታች ዋንጫ ማጣሪያ ከዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ አቻው ጋር ዛሬ ያደረገው ጨዋታ ያለ ምንም ግብ 0 ለ 0 ተጠናቀቀ፡፡
አንደኛ ዙር የመጀመሪያ ማጣሪያ ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የተካሄደ ሲሆን÷ ጨዋታው ያለምንም ግብ ተጠናቋል፡፡…
ከ23 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድኑ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ጨዋታውን ያደርጋል
አዲስ አበባ፣ መስከረም 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ከ23 ዓመት በታች ብሄራዊ ቡድን በአፍሪካ ከ 23 ዓመት በታች ዋንጫ ማጣርያ ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ዛሬ ጨዋታውን ያደርጋል፡፡
አንደኛ ዙር የመጀመሪያ ማጣሪያ ጨዋታው ዛሬ ከቀኑ 10 ሰዓት በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚደረግ መሆኑን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡…
ከብሄራዊ ቡድኑ ጋር በመቀጠሌ ደስተኛ ነኝ – አሰልጣኝ ውበቱ አባተ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 9፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ከብሄራዊ ቡድኑ ጋር በመቀጠሌ ደስተኛ ነኝ ሲሉ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን አሰልጣኝ ውበቱ አባተ ተናገሩ፡፡
አሰልጣኙ ባሳለፍነው ዓርብ ተጨማሪ የሁለት ዓመት ውል ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ጋር መፈራረማቸውን ተከትሎ በዛሬው ዕለት ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡
አሰልጣኝ ውበቱ በመግለጫቸው÷ እስከ መስከረም 2017…
በሲድኒ የሴቶች ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ መስከረም 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውስትራሊያ ሲድኒ በተደረገ የሴቶች ማራቶን ውድድር ኢትዮጵውያን አትሌቶች በፍጽም የበላይነት አሸንፈዋል፡፡
አትሌት ትዕግስት ግርማ ርቀቱን 2 ሰዓት 25 ደቂቃ ከ10 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በመጨረስ ወድድሩን በአንደኛነት አጠናቃለች፡፡
ሌላኛው ኢትዮጵያዊ አትሌት ለተብርሃን ሀይላይ ርቀቱን 2 ሰዓት ከ25 ደቂቃ 45…