Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ከ20 ዓመት በታች በ5ሺህ ሜትር ሴቶች ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1 እስከ 3 በመውጣት ድል አደረጉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛምቢያ ንዶላ ከ20 ዓመት በታች ሻምፒዮና ማጠቃለያ ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ከ1 እስከ 3 በመውጣት ድል አድርገዋል፡፡ አትሌት ውብርስት አስቻለ ቀዳሚ በመሆን ለሀገሯ ወርቅ ስታስገኝ፣ አይናዲስ መብራቴ 2ኛ በውጣት ብር እንዲሁም   አስማረች አንለይ 3ኛ በውጣት ነሃስ አስገኝተዋል፡፡ በውድድሩ ኢትዮጵያ 7 የወርቅ በአጠቃላይ ደግሞ 23 ሜዳሊያዎችን መሰብሰብ ችላለች፡፡
Read More...

የአፍሪካ ከ18 እና ከ20 አመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጠናቀቃል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 25፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛምቢያ ንዶላ ሲካሄድ የቆየው 2ኛው የአፍሪካ ከ18 እና ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ ይጠናቀቃል፡፡ በሻምፒዮናው መዝጊያ ዕለት የቡድን 5 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ጾታዎች በተለያዩ ርቀቶች ይሳተፋሉ፡፡ አሁን ላይ ከ18 አመት በታች የሴቶች 5 ሺህ ሜትር የእርምጃ ውድድር  አበቡ አያሌው ሁለተኛ…

በፕሪሚየር ሊጉ ኢትዮጵያ ቡና እና አዳማ ከተማ ነጥብ ተጋርተዋል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የ22ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር የሁለተኛ ቀን ውሎ ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና እና አዳማ ከተማ 2 ለ 2 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡ መሐመድ ኑር ናስር ለኢትዮጵያ ቡና ሁለቱንም ግቦች ሲያስቆጥር÷…

ሻሸመኔ ከተማ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መመለሱን አረጋገጠ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ሻሸመኔ ከተማ የአዲስ አበባ ከተማን ሽንፈት ተከትሎ ከ15 የውድድር ዘመናት በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መመለሱን አረጋግጧል፡፡ ሻሸመኔ ከተማ ለመጨረሻ ጊዜ በሀገሪቱ ትልቁ ሊግ ተሳትፎ ያደረገው በ2000 ሚድሮክ ሚሌኒየም ፕሪሚየር ሊግ ላይ ነበር።

የእርምጃ ተወዳዳሪው አትሌት ምስጋና ዋቁማ ለሀገሩ ወርቅ አስገኘ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በዛምቢያ እየተካሄደ በሚገኘው ከ20 ዓመት በታች የእርምጃ ውድድር ኢትዮጵያ በአትሌት ምስጋና ዋቁማ ወርቅ አገኘች፡፡ አትሌት ምስጋና ዋቁማ በ10 ሺህ ሜትር የእርምጃ ውድድር አንደኛ ሆኖ በማጠናቀቁ ነው ለሀገሩ የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው፡፡ በዛምቢያ ንዶላ የአፍሪካ ከ20 እና ከ18 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና…

ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2015 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ሻምፒዮን ሆነ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2015 የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግን ለተከታታይ ሦስተኛ ጊዜ አሸንፏል። በ25 ሳምንት የሊጉ መርሃግብር ይርጋጨፌ ቡናን የገጠመው ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሎዛ አበራ ሃትሪክ እና በመሳይ ተመስገን አንድ ግብ 4 ለ 0 በመርታት አንድ ጨዋታዎች እየቀረው የሊጉ አሸናፊ መሆኑን አረጋግጧል።…

በፕሪሚየርሊጉ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ድል ቀንቷቸዋል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ፋሲል ከነማ እና ወላይታ ድቻ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡ በሊጉ ተጣባቂ የነበረው የፋሲል ከነማ እና ሀድያ ሆሳዕና ጨዋታ በፋሲል ከነማ 2 ለ 1 አሸነፊነት ተጠናቋል፡፡ አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ…