ስፓርት
ከተማ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 7ኛው ከተማ አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ “አዲስ አበባ የሰላምና የአብሮነት ከተማ” በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ተካሄደ።
በክፍለ ከተማው መድሃኔአለም አደባባይ ላይ በተካሄደው ስፖርታዊ እንቅስቃሴ የከተማ አስተዳድሩ ምክትል ከንቲባ አቶ ጃንጥራር አባይ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ተሳትፈዋል።
በዕለቱ መልዕክት ያስተላለፉት አቶ ጃንጥራር አባይ ፥ ስፖርት አይቋረጥምና የዘወትር ስራችን አድርገን ጤናማ ማህበረሰብ ለመፍጠር መትጋት ይኖርብናል ብለዋል።
የክፍለ ከተማው ዋና…
Read More...
ኢትዮ-ሰላም ሩጫ በወላይታ በሚል መሪ ቃል በወላይታ ሶዶ የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሄደ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4፣2014 (ኤፍ ቢሲ) ኢትዮ-ሰላም ሩጫ በወላይታ በሚል መሪ ቃል በወላይታ ሶዶ የጎዳና ላይ ሩጫ ተካሄዷል፡፡
ሩጫው የፌደራልና የክልል ከፍተኛ የመንግስት የስራ ኃላፊዎችና ታላላቅ አትሌቶች በተገኙበት ተካሂዷል ።
የጎዳና ላይ ሩጫው 5 ኪሎ ሜትር መንገድ የሸፈነ ሲሆን፥ ገቢውም የቀድሞውን ዳሞታ አትሌቲክስ ቡድንን መልሶ ለማቋቋም ይውላል ተብሏል።…
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ወደ ሀገር ቤት ተመልሷል
አዲስ አበባ፣ሰኔ 3፣2014 (ኤፍ ቢሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ውድድር መልስ ወደ አዲስ አበባ ተመልሷል።
ብሄራዊ ቡድኑ በሳምንታት ቆይታው በማላዊ 2 ለ 1 ቢሸነፍም ግብጽን 2 ለ 0 በማሸነፍ በግብ ክፍያ በልጦ የምድቡ አናት ላይ መቀመጥ ችሏል።
ዋሊያዎቹ ወደ አዲስ አበባ ከመመለሳቸው በፊት በማላዊዉ ካሙዙ ኤርፖርት የኢትዮጵያ የአየር መንገድ…
በአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ3 ሺህ ሜትር የወንዶች መሠናክል ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በሞሪሺየስ እተካሄደ በሚገኘው የ22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ቀንቷቸዋል፡፡
ዛሬ በተደረገው የ3 ሺህ ሜትር መሠናክል ወንዶች ውድድር አትሌት ሃይለማሪያም አማረ እና አትሌት ታደሰ ታከለ 1ኛ እና ሁለተኛ በመሆን የወርቅና የብር ሜዳልያ ለአገራቸው ማስገኘታቸውን ከአትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው…
በ22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን የወርቅና የብር ሜዳልያዎች አገኘች
አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 1 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ የመጀመሪያዎቹን የወርቅና የብር ሜዳልያዎች አገኘች።
ሜዳልያዎቹ በ10 ሺህ ሜትር ወንዶች የተገኘ ነው።
በውድድሩ አትሌት ሞገስ ጥኡማይ እና አትሌት ጭምዴሳ ደበላ ተከታትለው በመግባት ለሃገራቸው ሜዳልያዎቹን ማስገኘታቸውን የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌደራሽን መረጃ ያመላክታል።…
22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 1፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሞሪሺየስ የሚካሄደው 22ኛው የአፍሪካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ተጀምሯል።
ኢትዮጵያ በሻምፒዮናው 28 ሴት እና 26 ወንድ በድምሩ 54 አትሌቶችን የምታሳትፍ ሲሆን÷በመክፈቻው ቀን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ የማጣሪያ ውድድሮች ይካፈላሉ።
በ100 ሜትር ሴቶች ራሔል ተስፋዬ እና ያብስራ ጃርሶ፣ በ400 ሜትር ሴቶች ፅጌ…
በሴቶች የሴካፋ ዋንጫ ሉሲዎቹ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቀሉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በምስራቅና መካከለኛው አፍሪካ ሴቶች (ሴካፋ) ዋንጫ ሉሲዎቹ ግማሽ ፍፃሜውን ተቀላቅለዋል፡፡
ዛሬ በተደረገ የሴቶች የሴካፋ ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ሉሲዎቹ ደቡብ ሱዳንን 4 ለ 0 ረተዋል፡፡
በጨዋታው አረጋሽ ካልሳ ሶስት ግቦችን በማስቆጠር ሃት - ትሪክ ስትሰራ ሎዛ አበራ አንደኛውን ጎል ማስቆጠር ችላለች፡፡…