ስፓርት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለቻን ውድድር አልጄሪያ ገብቷል
አዲስ አበባ፣ ጥር 4፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የቻን ውድድር አስተናጋጅ በሆነችው አልጄርያ በሰላም ገብቷል፡፡
ብሄራዊ ቡድኑ አልጀርስ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስ በአልጀርያ ባህላዊ ሙዚቃ የታጀበ አቀባበል ተደርጎለታል።
ዋልያዎቹ በቻን ውድድር በምድብ አንድ ከአዘጋጇ አልጄሪያ እንዲሁም ሞዛምቢክ እና ሊቢያ ጋር ተደልድለዋል።
ኢትዮጵያ የመጀመሪያ ጨዋታዋን ጥር 6 ቀን 2015 ዓ.ም ከሞዛምቢክ ጋር የምታደርግ ይሆናል፡፡
በሀገር ውስጥ ሊግ የሚገኙ…
Read More...
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አልጄሪያ አቀና
አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአልጄሪያ አስተናጋጅነት በሚካሔደው ሰባተኛው የአፍሪካ እግር ኳስ ሻምፒዮና (ቻን) የሚሳተፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ወደ አልጀሪያ አቀና፡፡
ውድድሩ ከነገ በስቲያ ይጀመራል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለውድድሩ በአገር ውስጥ እና ከአገር ውጪ ቅድመ ዝግጅት አድርጓል።
ዋልያዎቹ በቻን ውድድር በምድብ አንድ ከአዘጋጇ…
የሴቶች ፕሪሚየር ሊግና የሴቶች ከፍተኛ ሊግ 2ኛ ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን ይፋ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ፣ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ እና ከ20 ዓመት በታች ፕሪሚየር ሊግ ሁለተኛ ዙር ውድድር የሚጀመርበት ቀን እና የዝውውር ጊዜ ይፋ ተደርጓል።
በዚህ መሰረትም የሴቶች ፕሪሚየር ሊግ እና ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ሁለተኛ ዙር ውድድር የካቲት 26 ቀን2015 ዓ.ም እንደሚጀመር ተገልጿል፡፡
…
አሸናፊ በቀለ የፋሲል ከነማ አሰልጣኝ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) አሸናፊ በቀለ የፋሲል ከነማ አሰልጣኝ በመሆን አፄዎቹን በይፋ ተረክበዋል፡፡
ፋሲል ከነማ በዘንድሮው የሊግ ውድድር ደካማ አቋም ያሳየ ሲሆን ፥ ባደረጋቸው 13 ጨዋታዎች 17 ነጥቦችን ብቻ በመሰብሰብ 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡
በዚህም ክለቡ የቡድኑን አሰልጣኝ ሀይሉ ነጋሽን ቀደም ብሎ ያሰናበተ ሲሆን ፥ በምትኩ አሰልጣኝ…
ዋሊያዎቹ በአቋም መፈተሻ ጨዋታ በሞሮኮ አቻቸው 2 ለ 1 ተሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በሁለተኛ ዙር የአቋም መፈተሻ ጨዋታ በሞሮኮ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፏል፡፡
የቻን ዝግጅቱን በሞሮኮ ካዛብላንካ በማድረግ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሁለተኛ የወዳጅነት ጨዋታውን በዛሬው ዕለት ከሞሮኮ አቻው ጋር ራባት በሚገኘው መሐመድ 6ኛ አካዳሚ አድርጓል፡፡
በጨዋታውም የኢትዮጵያ…
ጋሬዝ ቤል ከእግር ኳስ ሕይወትራሱን አገለለ
አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ዌልሳዊው ኢንተርናሽናል ጋሬዝ ቤል ራሱን ከክለብና ከብሄራዊ ቡድን ማግለሉን አስታውቋል፡፡
ቤል በማህበራዊ ትስስር ገጹ ባሰፈረው ጽሑፍ÷ “የምወደውን የእግር ኳስ ስፖርት የመጫወት ህልሜን በማሳካቴ እድለኛ ነኝ ፤ነገር ግን ከዚህ በላይ በእግር ኳስ ሕይወት አልቀጥልም ብሏል፡፡”
የቀድሞው የቶተንሃም እና…
ሮቤርቶ ማርቲኔዝ የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ጥር 1፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የቀድሞው የቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሆኑ፡፡
ስፔናዊው አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ÷ በዓለም ዋንጫው የተሰናበቱትን አሰልጣኝ ፈርናንዶ ሳንቶስ በመተካት ነው በዛሬው ዕለት የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የሆኑት፡፡
የፖርቹጋል እግር ኳስ ፌደሬሽን ፕሬዚዳንት ፈርናንዶ…