Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወልቂጤ ከተማ ጅማ አባጅፋርን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ29ኛ ሣምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ረፋድ ላይ በተካሄደ ጨዋታ ወልቂጤ ከተማ ጅማ አባ ጅፋርን 3 ለ 0 አሸንፏል፡፡ የወልቂጤ ከተማን የአሸናፊነት ጎሎች÷ ዋህብ አዳምስ፣ በኃይሉ ተሻገር እና ጫላ ተሸታ አስቆጥረዋል፡፡ ክትፎዎቹ ማሸነፋቸውን ተከትሎ÷ ነጥባቸውን 35 በማድረስ ከሀዲያ ሆሳዕና ጋር 8ኛ ደረጃ ላይ መቀመጥ ችለዋል፡፡ ጅማ አባ ጅፋር እና ሰበታ ከነማ ከቀናት በፊት ከፕሪሚየር ሊጉ መውረዳቸውን ማረጋገጣቸው ይታወሳል፡፡ …
Read More...

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር  ሊግ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ወላይታ ዲቻ ድል ቀንቶታል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ28ኛው ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ወላይታ ዲቻ ጅማ አባ ጅፋርን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ ረፋድ ላይ በተደረገው ጨዋታ ጅማ አባ ጅፋር በመሱድ መሀመድ ጎል እስከ እረፍት መምራት ቢችሉም ከረፍት መልስ አበባየሁ አጂሶ ባሰቆጠሯቸው ጎሎች ወላይታ ዲቻ ሙሉ 3 ነጥብ ማግኘት ችሏል፡፡ የጦና ንቦች…

በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ባህርዳር ከተማ ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) በ28ኛ ሳምንት በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየርሊግ ባህርዳር ከተማ ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ በሜዳው እና በደጋፊው ፊት ጨዋታውን ላደረገው ባህርዳር ከተማ መናፍ አወል ብቸኛዋ የማሸነፊያ ጎል ማስቆጠር ችሏል፡፡ የጣና ሞገዶቹ ዘሬ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ነጥባቸውን 33 በማድረስ ከወራጅ ቀጠና ሸሽተዋል፡፡…

ፋሲል ከነማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ በካፍ የክለቦች ውድድር ኢትዮጵያን ይወክላሉ

አዲስ አበባ፣ሰኔ 13፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተደረገ ጨዋታ ፋሲል ከነማ አዳማ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ረፋድ በተደረገው ጨዋታ የፋሲልን የማሸነፊያ ጎሎች ሙጂብ ቃሲም ከዕረፍት መልስ አስቆጥሯል፡፡ አጼዎቹ ዛሬ ማሸነፋቸውን ተከትሎ ነጥባቸውን 55 ያደረሱ ሲሆን ከቅዱስ ጊዮርጊስ ጋር ያላቸውን የነጥብ ልዩነት በማጥበብ በዋንጫ…

በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ 5 ሺህ ሜትር ውድድር ሰለሞን ባረጋ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ በ5 ሺህ ሜትር ውድድር ሰለሞን ባረጋ አሸንፏል፡፡ በወንዶች ምድብ በተካሄደው 5 ሺህ ሜትር የፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ሰለሞን ባረጋ ርቀቱን በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ÷ሙክታር እድሪስ ደግሞ 3ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡ በምድቡ አዲሱ ይሁኔ 5ኛ ሆኖ ውድድሩን የጨረሰ መሆኑንም ከአትሌቲክስ ፌደሬሽን…

በፕሪሚየር ሊጉ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልቂጤ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ27ኛ ሳምንት የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወልቂጤ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ረፋድ ላይ በባህር ዳር አለም አቀፍ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ከነዓን ማርክነህ በ25ኛ ደቂቃ እንዲሁም ጋቶች ፓኖም በ79ኛ ደቂቃ የቅዱስ ጊዮርጊስን የአሸናፊነት ግብ አስቆጥረዋል፡፡ ከሰዓት 10 ሰዓት ሀዋሳ ከተማ…