Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ክሪስታል ፓላስ አስቶን ቪላን በማሸነፍ ለኤፍ ኤ ካፕ ፍጻሜ አለፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ የኤፍ ኤ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ክሪስታል ፓላስ አስቶን ቪላን 3 ለ 0 በማሸነፍ የፍጻሜ ተፋላሚ መሆኑን አረጋግጧል፡፡ ምሽት 1፡15 በዌንብሌይ በተደረገው የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ የፓላስን የማሸነፊያ ግቦች ኤቤርቺ ኤዜ እና ኢስማኤላ ሳር (2) አስቆጥረዋል፡፡ በሌላ የግማሽ ፍጻሜ መርሐ ግብር ማንቸስተር ሲቲ ከኖቲንግሃም ፎረስት በነገው ዕለት የሚጫወቱ ሲሆን፥ ክሪስታል ፓላስ ከሁለቱ ክለቦች አሸናፊ ጋር ለፍጻሜ ይፋለማል፡፡
Read More...

ወላይታ ድቻ በኢትዮጵያ ዋንጫ ለፍጻሜ አለፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ዋንጫ የግማሽ ፍጻሜ ጨዋታ ወላይታ ድቻ ሸገር ከተማን 2 ለ 0 በማሸነፍ ለሁለተኛ ተከታታይ ጊዜ ወደ ፍጻሜ ማለፉን አረጋግጧል፡፡ ወላይታ ድቻ ለቀጣዩ የውድድር ዓመት ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ያደገውን ሸገር ከተማን ባሸነፈበት ጨዋታ ዘላለም አባተ እና ብዙዓየሁ ሰይፈ የማሸነፊያ ግቦችን አስቆጥረዋል፡፡…

በጀርመን በተካሄደው የአዲዳስ ውድድር ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በዛሬው ዕለት በጀርመን በተካሄደው የአዲዳስ አዲዜሮ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ድል ተቀዳጅተዋል። በ5 ኪሎ ሜትር ሴቶች ውድድር አትሌት መዲና ኢሳ ስታሸንፍ÷ በወንዶቹ ዮሚፍ ቀጀልቻ በቀዳሚነት አጠናቀዋል። ከፍተኛ ፉክክር በተደረገበት የሴቶች 5 ኪሎ ሜትር ውድድር የሁለት ዓመታት አሸናፊዋ አትሌት መዲና ኢሳ…

በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል አትሌት ሳሙኤል ፍሬው አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 18፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በወንዶች የ3 ሺህ ሜትር የመሰናክል ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ሳሙኤል ፍሬው አሸንፏል። በቻይና ዢያሚንግ ውድድር አትሌት ሳሙኤል በ8:05.61 በመግባት የቦታው ክብረወሰንና የዓመቱ የርቀቱ ፈጣን ሠዓት በማስመዝገብ በድንቅ ብቃት በበላይነት ማሸነፍ ችሏል። ሞሮኳዊው የኦሎምፒክ ሻምፒዮን አትሌት ኤልባካሊን ሁለተኛ…

ከ13 ዓመታት ቆይታ በኋላ ከሌስተር ሲቲ ጋር የሚለያየው ጄሚ ቫርዲ…

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የሌስተር ሲቲ የፊት መስመር ተጨዋች ጄሚ ቫርዲ ከ13 ዓመታት ቆይታ በኋላ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከሌስተር ሲቲ ጋር እንደሚለያይ ክለቡ አስታውቋል፡፡ ሌስተር ሲቲ በፈረንጆቹ 2015/16 የውድድር ዓመት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ሲያሳካ የቫርዲ አስተዋፅኦ ከፍተኛ እንደነበር ይታወሳል፡፡ ጄሚ ቫርዲ ሌስተር ሲቲን…

አርሰናልና ክሪስታል ፓላስ ዛሬ ምሽት ጨዋታቸውን ያደርጋሉ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርሰናል በሜዳው ኤሚሬትስ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ክሪስታል ፓላስን ያስተናግዳል። በ66 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አርሰናል ከተከታዮቹ ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማስጠበቅ ከጨዋታው ሙሉ ሶስት ነጥብ ለማግኘት ይፋለማል። በኦሊቨር ግላስነር የሚመራው ክሪስታል ፓላስ…

“የአሮን ራምሴ እርግማን “

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 15፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ዌልሳዊው ኢንተርናሽናል የአርሰናል የቀድሞ አማካኝ ተጫዋች አሮን ራምሴ ግብ በሚያስቆጥርባቸው አጋጣሚዎች ሁሉ አንድ የዓለማችን ገናና ሰው በሠዓታት ልዩነት ሕይዎቱ ያልፋል፡፡ ይህን አጋጣሚ በተደጋጋሚ ያስተዋሉ ጋዜጠኞችም፤ “የአሮን ራምሴ እርግማን (ዘ ከርስ ኦፍ አሮን ራምሴ)” ሲሉ ይጠሩታል፡፡ አሮን ራምሴ ግብ…