ስፓርት
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ9ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሃ ግብር ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
ምሽት 1 ሰዓት 30 ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ በሜዳው ኦልድትራፎርድ ብራይተንን የሚያስተናግድበት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ከረጅም ጊዜ በኋላ ተከታታይ ሁለት ጨዋታዎችን በሊጉ ያሸነፈው ማንቼስተር ዩናይትድ አሸናፊነቱን ለማስቀጠል ይፋለማል።
ሁለቱ ቡድኖች እርስ በርስ ካደረጓቸው ያለፉት አምስት ጨዋታዎች ብራይተን አራቱን በማሸነፍ የበላይነቱን የያዘ ሲሆን ማንቼስተር ዩናይትድ በአንዱ ድል አድርጓል፡፡…
Read More...
አስራት ኃይሌ ጎራዴው ሲታወስ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 15፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ ደማቅ አሻራ ፅፈው ካለፉ ሰዎች መካከል ነው አስራት ኃይሌ ጎራዴው፡፡
ለእግር ኳስ ልዩ ፍቅር የነበረው አስራት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ምንም ሳይሰስት ሁሉን ነገር ያደረገ እና የኢትዮጵያ እግር ኳስን ለማሳደግ ትልቅ አስተዋፅኦ ያበረከተ ልዩ ሰው ነበር።
አስራት ኃይሌ በተጨዋችነት እና…
አርባ ምንጭ ከተማ እና ባህር ዳር ከተማ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 14፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሁለተኛ ሳምንት የሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባ ምንጭ ከተማ ባህር ዳር ከተማ 1 ለ 1 አቻ ተለያይተዋል፡፡
አርባ ምንጭ ከተማ ታምራት ኢያሱ በ76ኛው ደቂቃ ላይ ባስቆጠራት ግብ ሲመራ ቢቆይም በጨዋታው መገባደጃ ግርማ ዲሳሳ ባህር ዳር ከተማን አቻ ማድረግ ችሏል፡፡
በአሁኑ ሰዓት መቐለ 70…
ስኮት ካርሰን ጓንቱን ሰቀለ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ውሉ በመጠናቀቁ ከማንቼስተር ሲቲ ጋር የተለያየው ስኮት ካርሰን ጓንቱን መስቀሉን ይፋ አድርጓል፡፡
በማንቼስተር ሲቲ ቤት ስድስት ዓመታት መቆየት የቻለው ግብ ጠባቂው ስኮት ካርሰን በ40 ዓመቱ ነው ጓንቱን የሰቀለው፡፡
ስኮት ካርሰን በሲቲ በቆየባቸው 6 ዓመታት የፕርሚየር ሊግ እና…
ሊዮኔል ሜሲ በኢንተር ሚያሚ ለመቆየት ውሉን አራዘመ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አርጀንቲናዊው ተጫዋች ሊዮኔል ሜሲ በኢንተር ሚያሚ ቤት ለመቆየት ውሉን ማራዘሙ ይፋ ተደርጓል፡፡
የስምንት ጊዜ የባሎን ዶር አሸናፊው ሊዮኔል ሜሲ በኢንተር ሚያሚ እስከ ፈረንጆቹ 2028 ለመቆየት ነው ውሉን ያራዘመው፡፡
የ38 ዓመቱ ሊዮኔል ሜሲ ለቀጣይ ሶስት ዓመታት በአሜሪካው ክለብ ኢንተር ሚያሚ የሚጫወት ይሆናል፡፡…
ፋሲል ከነማ ድል ሲቀናው አዳማ ከተማ አቻ ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የፋሲል ከነማን የማሸነፊያ ግቦች በረከት ግዛው እና አቤኔዘር ዮሀንስ አስቆጥረዋል፡፡
ፋሲል ከነማ ወደ ድል ሲመለስ ወልዋሎ ዓዲግራት…
ኢትዮጵያ ቡና ነገሌ አርሲን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 13፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሁለተኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና ነገሌ አርሲን 2 ለ1 አሸንፏል፡፡
የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች አቡበከር አዳሙ እና በፍቃዱ አለማየሁ አስቆጥረዋል፡፡
ነገሌ አርሲን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ ደግሞ ገ/መስቀል ዱባለ ከመረብ አሳርፏል፡፡
የሊጉ መርሐ ግብር…