ስፓርት
የኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ በድጋሚ ተራዘመ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የ25ኛ ሣምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ መርሐ-ግብር የነበረው የኢትዮ ኤሌክትሪክ እና ድሬዳዋ ከተማ ጨዋታ በድጋሚ ተራዝሟል፡፡
በሐዋሳ ከተማ በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት ጨዋታው በዕለቱ ሳይደረግ ተራዝሞ የነበረው ጨዋታ ዛሬ ደግሞ 84ኛ ደቂቃ ላይ የስታዲየሙ መብራት ሊበራ ባለመቻሉ ጨዋታው ተቋርጦ በድጋሚ ተራዝሟል፡፡
ጨዋታውን ኢትዮ ኤሌክትሪክ በሽመክት ጉግሳ እና አሸናፊ ጥሩነህ ግቦች 2 ለ 0 እየመራ ነበር።
የቀሪዎቹ ደቂቃዎች ጨዋታ በውድድር ደንቡ መሠረት ነገ ሚያዝያ…
Read More...
ማንቼስተር ዩናይትድ ከበርማውዝ ጋር አቻ ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማንቼስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከበርንማውዝ ጋር ያደረገውን ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ውጤት አጠናቅቋል፡፡
የበርንማውዝን ግብ ሴሜኒዮ በመጀመሪያው አጋማሽ ሲያስቆጥር፤ ሆይሉንድ ማንቼስተር ዩናይትድን አቻ ያደረገች ግብ በጨዋታው መጠናቀቂያ ከመረብ አሳርፏል፡፡…
ሲዳማ ቡና በኢትዮጵያ ዋንጫ ለፍጻሜ አለፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ዋንጫ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ሲዳማ ቡና መቻልን በመለያ ምት 7 ለ 6 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ ሲዳማ ቡና በፍፃሜው ከወላይታ ድቻ ጋር ይገናኛል፡፡
ወላይታ ድቻ ትናንት በግማሽ ፍፃሜው ሸገር ከተማን በማሸነፍ ለፍጻሜ መብቃቱ ይታወቃል፡፡
የዛሬው የሲዳማ ቡና እና መቻል ጨዋታ መደበኛ ክፍለ…
በጃፓን በተካሄደ የግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ዳዊት ወልዴ አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በጃፓን ጊፉ ከተማ በተካሄደ የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ዳዊት ወልዴ አሸንፏል፡፡
ውድድሩን 1፡00፡06 በሆነ ሰዓት በመግባት በአንደኝነት ያጠናቀቀው አትሌት ዳዊት ወልዴ፤ በውድድሩ ሲሳተፍ የመጀመሪያው እንደሆነ ተገልጿል።
በሴቶች በተካሄደው ውድድር ደግሞ ኢትዮጵያዊቷ ጎይተይቶም ገብረስላሴ 1:08:29…
በሴቶች የለንደን ማራቶን አትሌት ትዕግስት አሰፋ አሸነፈች
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ45ኛው የለንደን ማራቶን በሴቶች ምድብ የፓሪስ ኦሊምፒክ የብር ሜዳሊያ ባለቤቷ አትሌት ትዕግስት አሰፋ በአንደኝነት አጠናቅቃለች፡፡
አትሌት ትግስት ርቀቱን ለመጨረስ 2 ሠዓት ከ15 ደቂቃ ከ50 ሠከንድ ፈጅቶባታል፡፡
በዚሁ ውድድር መርሐ-ግብር ኬንያዊቷ አትሌት ጄፕኮስፔ ሁለተኛ እንዲሁም አትሌት ሲፋን ሀሰን ሦስተኛ…
ሊቨርፑል ሻምፒየንነቱን ቀድሞ ለማረጋገጥ አንድ ነጥብ ብቻ…
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ የሊጉ መሪ ሊቨርፑል በሜዳው አንፊልድ ሮድ ምሽት 12 ሠዓት ከ30 ቶተንሃም ሆትስፐርን ያስተናግዳል።
ሊጉን በ79 ነጥብ እየመራ የሚገኘው ሊቨርፑል ከዛሬው ጨዋታ አንድ ነጥብ ካገኘ ቀሪ አራት ጨዋታዎች እየቀሩት ሻምፒየን መሆኑን ያረጋግጣል።
ተጋጣሚው ቶተንሃም ሆትስፐር…
ማንቼስተር ሲቲ ከኖቲንግሀም ፎረስት የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 19፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ኤፍ ኤ ካፕ የግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ከኖቲንግሃም ፎረስት ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ማንቼስተር ሲቲ የውድድር ዓመቱን ያለ ዋንጫ ላለማጠናቀቅ በዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየት ይፋለማል።
ማንቼስተር ሲቲ በሩብ ፍፃሜው ቦርንመዝን በማሸነፍ ለግማሽ ፍፃሜው ሲበቃ ኖቲንግሀም…