ስፓርት
ሉሲዎቹ ደቡብ ሱዳንን 11 ለ0 አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 3፣ 2013(ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ደቡብ ሱዳንን 11 ለ0 አሸንፏል፡፡
ትናንት ምሸት በመብራት መቋረጥ ምክንያት 81ኛው ደቂቃ ላይ ቆሞ የነበረው የኢትዮጵያ እና ደቡብ ሱዳን ሴት ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ ዛሬ ረፋድ ላይ ቀሪ ደቂቃዎች ተደርጎ ኢትዮጵያ 2 ተጨማሪ ጎል አስቆጥራ 11 ለ 0 ተጠናቋል፡፡
በዛሬ ረፋዱ ጨዋታ ሎዛ አበራ 86ኛው እና 90ኛው ደቂቃ ላይ ከሴናፍ ዋቁማ የተመቻቹላትን ኳሶች አስቆጥራለች፡፡
ደቡብ ሱዳን ላይ 7 ጎሎች ያስቆጠረችው ሎዛ አበራ በኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን…
Read More...
ባህር ዳር ከተማ ወልቂጤ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ባህር ዳር ከተማ ወልቂጤ ከተማን 2 ለ 0 አሸነፈ፡፡
ዛሬ ከሰዓት የተካሄደው የቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ባህር ዳር ከተማን ከወልቂጤ ከተማ አገናኝቷል፡፡
በጨዋታውም ባህር ዳር ከተማ ወልቂጤ ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የባህር ዳር ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ባዬ ገዛኸኝና…
ሉሲዎቹ ከደቡብ ሱዳን አቻቸው ጋር የአቋም መለኪያ ጨዋታ ሊያደርጉ ነው
አዲስ አበባ ፣ ሚያዝያ 1 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን (ሉሲዎቹ) ከደቡብ ሱዳን አቻቸው ጋር የመጀመሪያውን የአቋም መለኪያ ጨዋታ ነገ በአዲስ አበባ ስታዲየም እንደሚያደርጉ ተገለፀ፡፡
ጨዋታው በአዲስ አበባ ስታዲየም እየተካሄደ በሚገኘው የሃገር አቀፍ የአትሌቲክስ ውድድር ምክንያት ነገ ከምሽቱ 12 ሠዓት ከ30 እንደሚደረግ…
በቤትኪንግ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታ ፋሲል ከነማ መሪነቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ዛሬ ምሽት በተካሄደው የቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ፋሲል ከነማ ወላይታ ድቻን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ፡፡
ፋሲል ከነማ ወላይታ ድቻን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት ነው ያሸነፈው፡፡
ለፋሲል ከነማ በመጀመሪያውና በሁለተኛው አጋማሽ ሁለቱንም ግቦች ሙጂብ ቃሲም አስቆጥሯል፡፡
ቀደም ብሎ 10 ሰዓት ላይ በተካሄደው ጨዋታ…
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ስድስት ደረጃዎችን አሻሻለ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 30፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ዓለም አቀፉ የእግር ኳስ አስተዳዳሪ አካል (ፊፋ) በሚያወጣው ወርሃዊ የሃገራት የእግር ኳስ ደረጃ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ስድስት ደረጃዎችን አሻሻለ፡፡
ቡድኑ በወርሃዊው የሃገራት ደረጃ ከነበረበት 146ኛ ደረጃ 140ኛ ላይ መቀመጡን ፊፋ ያወጣው መረጃ ያመለክታል፡፡
ብሔራዊ ቡድኑ ካሜሩን ለምታስተናግደው የአፍሪካ ዋንጫ…
ከእረፍት መልስ የተካሄደው የቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ የመጀመሪያ ጨዋታ በአቻ ውጤት ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በዓለም አቀፍ ደረጃ በነበሩ የሀገራት ጨዋታዎች ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የቤትኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በድሬዳዋ ጀምሯል።
ከእረፍት መልስ የመጀመሪያ በነበረው ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሰበታ ከተማ ያለምንም ግብ በአቻ ውጤት ተለያይተዋል።
በጨዋታው ሁለቱ ቡድኖች ግቦችን ለማግኘት ሙከራ ቢያደርጉም…
ኢትዮጵያ ቡና ኤርትራዊውን ሮቤል ተክለሚካኤልና ናትናኤል በርሔን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 29፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብን ሁለት ተጫዋቾችን ማስፈረሙን አስታውቋል።
ኢትዮጵያ ቡና የኤርትራ ብሔራዊ ቡድን አንበል እና የቀይ ባህር እግር ኳስ ክለብ ተጫዋች የነበረው እና የሴካፋ ሀገራት ውድድር ላይ የውድድሩ ኮከብ ተጫዋች ተብሎ የተመረጠውን ሮቤል ተክለሚካኤል ማስፈሙን ነው የገለፀው።
በተጨማሪም ለደደቢት…