Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ሴኔጋል እና ካሜሮን ለ2022 ዓለም ዋንጫ ማለፋቸውን አረጋገጡ

አዲስ አበባ፣መጋቢት 21፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሴኔጋል እና ካሜሮን ለ2022 ዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ተወካይ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡ የአፍሪካ ዋንጫ አሸናፊዋ ሴኔጋል በፍፃሜው ያገኘቻትን ግብፅን በድጋሚ በመለያ ምት በማሸነፍ ለኳታሩ 2022 ዓለም ዋንጫ ጨዋታ ማለፏን አረጋግጣለች። በመጀመሪያው ዙር ጨዋታ ሴኔጋል ካይሮ ላይ በግብፅ 1 ለ 0 በሆነ ውጤት መሸነፏ ይታወሳል። ትላንት በዳካር በተካሄደው የመልስ ጨዋታ ግብጻዊው ተከላካይ ሃምዲ ፋቲ በራሱ ላይ ባስቆጠራት ጎል በመደበኛው እና በተጨማሪው…
Read More...

16ኛ ሳምንት ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግ ነገ በአዳማ ይጀምራል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 20፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 16ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕርሚየር ሊግ ነገ በሚካሄዱ መርሃግብሮች ይጀምራል፡፡ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጅ ዩኒቨርሲቲ በሚደረገው ጨዋታ÷ 9 ሰዓት ላይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ከሰበታ ከተማ እንዲሁም 12 ሰዓት ላይ ደግሞ ፋሲል ከነማ ከሀዲያ ሆሳዕና ጨዋታቸውን ያደረጋሉ፡፡ የስታዲየም…

የአማራ ክልል ለቅድመ ዝግጅት ላወጣው ወጪ ካሳ እንደሚከፍል ፌዴሬሽኑ አስታወቀ

አዲስ አበባ፣መጋቢት 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ለ51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ቅድመ ዝግጅት የአማራ ክልል ላወጣው ወጪ ካሳ እንደሚከፍል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታወቋል፡፡ ፌዴሬሽኑ በደብዳቤ እንዳስታወቀው÷ 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና በባህርዳር ከተማ እንዲካሄድ ውሳኔ በማሳለፍ እንቅስቃሴ ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቋል፡፡…

በአትሌቲክስ ሻምፒዮና መከላከያና ኢትዮ ኤሌትሪክ ስፖርት ክለቦች የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያ አገኙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 19፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና መከላከያና ኢትዮ ኤሌትሪክ ስፖርት ክለቦች የመጀመሪያ የወርቅ ሜዳሊያ አግኝተዋል፡፡ ዛሬ በሲዳማ ክልል ሃዋሳ ስታዲየም በተካሄደው ውድድር÷ በሴቶች አሎሎ ውርወራ የመከላከያዋ አትሌት ዙርጋ ኡስማን 13 ነጥብ 56 ሜትር በመወርወር የወርቅ ሜዳሊያ አግኝታለች።…

አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው የዓለም የ10 ኪሎ ሜትር ክብረ ወሰንን ሰበረች

አዲ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በስፔን በተካሄደ የአለም አትሌቲክስ የጎዳና ላይ ሩጫ አትሌት ያለምዘርፍ የኋላው የዓለም የ10 ኪሎ ሜትር ክብረ ወሰንን በመስበር ጭምር ውድድሩን በበላይነት አጠናቀቀች፡፡ ከዓለም አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው፥ አትሌት ያለምዘርፍ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫን 29:14 በሆነ ጊዜ…

አትሌት ሙክታር ኢድሪስ በስፔን የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ ሪከርድ በማሻሻል ጭምር አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 18፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አትሌት ሙክታር ኢድሪስ በስፔን የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ሩጫ የቦታውን ሪከርድ በመስበር ጭምር አሸንፏል፡፡ አትሌቱ 28:34 በሆነ ጊዜ በመግባት ነው የቦታውን ሪከርድ ጭምር በማሻሻል መሸነፍ የቻለው፡፡ በተመሳሳይ በቱርክ ኢስታንቡል በተደረገ የግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ፀሐይ ገመቹ…

ኢትዮጵያዊው ፍቅሬ በቀለ በወንዶች የሮም ማራቶን አዲስ ክብረ ወሰን በማስመዝገብ አሸነፈ

አዲስ አበባ፣መጋቢት 18፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሮም የወንዶች ማራቶን ኢትዮጵያዊው ፍቅሬ በቀለ አዲስ ክብረ ወስን በማስመዝገብ አሸነፈ፡፡ አትሌቱ 2 ሰዓት ከ6 ደቂቃ ከ48 ሴኮንድ በሆነ ሰዓት አዲስ ክብረ ወሰን የሰበረ ሲሆን፥ ኬንያዊው ቤንጃሚን ኪፕቶ በ2009 ያስመዘገበውን ሪከርድ በመሰበር ነው ውድድሩን በበላይነት ያጠናቀቀው። አትሌት ታደሰ ማሞ ውድድሩን…