ስፓርት
ኢትዮ ኤሌክትሪክ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን መቀላቀሉን አረጋገጠ
አዲስ አበባ፣መጋቢት 18፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በከፍተኛ ሊግ ሲጫወት የቆየው ኢትዮ ኤሌክትሪክ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን መቀላቀሉን አረጋግጧል፡፡
በኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ጌዲዮ ዲላን ያስተናገደው ኢትዮ ኤሌክትሪክ እንዳልካቸው ይልቃል እና አቤል ሀብታሙ ባሰቆጠሯቸው ጎሎች 2 ለ 0 ማሸነፍ ችለዋል፡፡
የዛሬ ረፋዱን ውጤት ተከትሎም ኢትዮ ኤሌክትሪክ አንድ ጨዋታ እየቀረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግን መቀላቀሉን አረጋግጧል፡፡
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ!
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-…
Read More...
የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከጋና አቻው ጋር የመልስ ጨዋታውን ያደርጋል
አዲስ አበባ፣መጋቢት 18፣2014 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከጋና አቻው ጋር የሚያደርገውን የመልስ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ያከናውናል።
በአሰልጣኝ ፍሬው ሀይለገብርኤል የሚመራው ብሄራዊ ቡድኑ ምሽት 12 ሰዓት ለሚካሄደው የመልስ ጨዋታ ወደ አክራ በማቅናት ዝግጅቱን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡
ብሄራዊ ቡድኑ አዲስ አበባ አበበ ቢቂላ ስታዲየም…
የቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ የሆነው አዳማ ከተማ የ60 ሚለየን ብር የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ፈረመ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) አዳማ ከተማ ከተለያዩ ኩባንያዎች ጋር የ60 ሚለየን ብር የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ማድረጉን አስታወቀ፡፡
የቤት ኪንግ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተሳታፊ የሆነው አዳማ ከተማ ከአንበሳ ቢራ እና ዋሊን ቢራ አምራች ኩባንያ ጋር የስፖንሰር ሺፕ ስምምነት ተፈራርሟል ።
የስፖንሰር ሺፕ ስምምነቱ የአምስት ዓመት መሆኑን…
የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ከኮሞሮስ አቻው ጋር ነገ የወዳጅነት ጨዋታ ያደርጋል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ወንዶች ብሔራዊ ቡድን ከኮሞሮስ አቻው ጋር ነገ የወዳጅነት ጨዋታ እንደሚያደርግ ተገለጸ።
የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ 10 ሺህ 725 ተመልካቾች በሚያስተናግደው “ስታድ ኦምኒስፖርትስ ደ ማሉንዚ” ይካሄዳል።
በአሠልጣኝ ውበቱ አባተ የሚመራው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን…
51ኛው የአትሌቲክስ ሻምፒዮና የፊታችን መጋቢት 19 ጀምሮ በሃዋሳ ይካሄዳል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 15፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) 51ኛው የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከመጋቢት 19 እስከ 24 ቀን 2014 ዓ.ም በሲዳማ ክልል ሃዋሳ ከተማ እንደሚካሄድ የአትሌቲክስ ፌዴሬሽን አስታወቀ።
በሻምፒዮናው ላይ የክልሎች፣ የከተማ አስተዳደሮች፣ የክለቦችና በአትሌቲክስ ማሰልጠኛ ማዕከላት የሚገኙ አትሌቶች ይሳተፋሉ ተብሏል።…
በቤልግሬድ የዓለም የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 14፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በ18ኛው የዓለም አትሌቲክስ የቤት ውስጥ ሻምፒዮና የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልኡካን ቡድን አዲስ አበባ ገባ።
የልዑካን ቡድኑ ዛሬ ጠዋት ቦሌ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ሲደርስም የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጄላ መርዳሳ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዚዳንት አትሌት ደራርቱ ቱሉን ጨምሮ…
የኢትዮጵያ የወንዶች የቮሊቦል ጥሎ ማለፍ ውድድር መጋቢት 15 ይጀመራል
አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የ2014 ዓ.ም የኢትዮጵያ የወንዶች የቮሊቦል ጥሎ ማለፍ ውድድር መጋቢት 15 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ቮሊቦል ፌዴሬሽን አስታወቀ።
በአዲስ አበባ ትንሿ ስታዲየም በሚካሄደው ውድድር ወላይታ ዲቻ፣ ሙገር ሲሚንቶ፣ መደወላቡ ዩኒቨርሲቲ፣ ብሔራዊ አልኮል፣ አዲስ አበባ ፖሊስ፣ መከላከያ እና…