ስፓርት
ሸገር ከተማ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ አሸናፊ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አስቀድሞ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ማደጉን ያረጋገጠው ሸገር ከተማ የሴቶች እግር ኳስ ቡድን የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ አሸናፊ ሆኗል፡፡
የከፍተኛ ሊጉ የ26ኛ ሳምንት እና የውድድር ዓመቱ የማጠቃለያ መርሐ ግብሮች የተደረጉ ሲሆን÷ ቀን 8 ሰዓት ላይ ሸገር ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና 3 አቻ ተለያይተዋል።
ውጤቱን ተከትሎ በሊጉ 64 ነጥብ የሰበሰበው ሸገር የሴቶች ቡድን ውድድሩን በበላይነት በማጠናቀቅ ሻምፒዮን መሆን ችሏል፡፡
ይርጋጨፌ ቡና ሴቶች ቡድን 54 ነጥብ በመያዝ 2ኛ ደረጃን…
Read More...
ክሪስታል ፓላስ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን አነሳ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኤፍኤ ካፕ የፍጻሜ ዋንጫ ጨዋታ ክሪስታል ፓላስ ማንቼስተር ሲቲን በማሸነፍ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን አንስቷል፡፡
በግዙፉ የእንግሊዝ ዌምብሌይ ስታዲየም የተካሄደውን የኤፍኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ክሪስታል ፓላስ 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
የፔፕ ጓርዲዮላ ቡድን ከፍተኛ የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የነበረው ቢሆንም…
ኢትዮጵያ መድን መቐለ 70 እንደርታን በማሸነፍ መሪነቱን አጠናከረ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 30ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን መቐለ 70 እንደርታን 1 ለ 0 በማሸነፍ መሪነቱን አጠናክሯል፡፡
ቀን 10 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ አቡበከር ሳኒ የኢትዮጵያ መድንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ከመረብ አሳርፏል፡
ውጤቱን ተከትሎም ኢትዮጵያ መድን ነጥቡን ወደ 60 ከፍ በማድረግ ለዋንጫ…
የኤፍኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት ይደረጋል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 9፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኤፍኤ ካፕ የፍጻሜ ጨዋታ ማንቼስተር ሲቲ ከክሪስታል ፓላስ ዛሬ ምሽት የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል።
የፍጻሜ ጨዋታው ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ላይ በእንግሊዝ ዌምብሌይ ስታዲየም ነው የሚካሄደው፡፡
ውሃ ሰማያዊዎቹ ለ8ኛ ጊዜ የኤፍኤ ካፕ ዋንጫን ለማሸነፍ ወደ ሜዳ የሚገቡ ሲሆን÷ክሪስታል ፓላሶች ደግሞ በታሪክ ለመጀመሪያ…
ሀዋሳ ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የሀዋሳ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች እስራኤል እሸቱ እና አሊ ሱሌማን ሲያስቆጥሩ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ቢኒያም ፍቅሬ ከመረብ አሳርፏል፡፡
የሀዋሳ ከተማ የፊት መስመር ተጨዋች አሊ ሱሌማን በውድድር ዓመቱ ያስቆጠራቸውን…
ሲዳማ ቡና ወላይታ ድቻን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ30ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ወላይታ ድቻን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የሲዳማ ቡናን የማሸነፊያ ብቸኛ ግብ ማይክል ኪፕሩቪል በመጀመሪያው አጋማሽ ከመረብ አሳርፏል፡፡
ሲዳማ ቡና ተከታታይ ሁለተኛ ድሉን ሲያስመዘግብ ወላይታ ድቻ በበኩሉ ሁለተኛ ተከታታይ ሽንፈቱን አስተናግዷል፡፡…
ክሪስቲያኖ ሮናልዶ ለተከታታይ 3ኛ ዓመት የዓለማችን ቁጥር አንድ ተከፋይ ስፖርተኛ ሆነ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 8፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የ40 ዓመቱ ፖርቹጋላዊ ኢንተርናሽናል ለተከታታይ ለሦስተኛ ዓመት የዓለማችን ቁጥር አንድ ተከፋይ ስፖርተኛ መሆን ችሏል፡፡
በአሁኑ ወቅት ለሳዑዲው ክለብ አልናስር እየተጫወተ የሚገኘው ክሪስቲያኖ ሮናልዶ፤ በዓመት 275 ሚሊየን ዶላር የሚከፈለው የምድራችን ቁጥር አንድ ስፖርተኛ መሆኑን የፎርብስ መጽሔት መረጃ አመላክቷል፡፡…