ስፓርት
አትሌት በሪሁ አረጋዊ የ10 ኪሎ ሜትር ክብረ ወሰንን ሰበረ
አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በስፔን ማድሪድ በተካሄደ ሳን ሲልቬስተር 2024 የ10 ኪሎ ሜትር ውድድር አትሌት በሪሁ አረጋዊ አዲስ ክበረወሰን በመስበር አሸንፏል፡፡
አትሌት በሪሁ ርቀቱን 26 ደቂቃ ከ32 ሰከንድ በሆነ ሰዓት በማጠናቀቅ ነው ክብረ ወሰን በማሻሻል ያሸነፈው፡፡
ኡጋንዳዊው አትሌት ጃኮብ ኪፕሊሞ በአንድ ሰከንድ ዘግይቶ በመግባት ሁለተኛ ደረጃን ሲይዝ÷ ስፔናዊው አዴል ሚካኤል ደግሞ ሶስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቅቋል፡፡
የ10 ኪሎ ሜትር ክበረ ወሰን በኬንያዊው አትሌት ሮኔክስ ኪፑሩቶ ተይዞ የነበረ ሲሆን÷…
Read More...
የኢትዮጵያ ክለቦች አትሌቲክስ ሻምፒዮና መካሄድ ጀመረ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ክለቦች የአጭር፣ መካከለኛ፣ የ3 ሺህ ሜትር መሰናክል የርምጃ እና የሜዳ ተግባራት አትሌቲክስ ሻምፒዮና ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡
ዛሬ በተካሄደው የሴቶች የርዝመት ዝላይ የፍፃሜ ውድድርም÷ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አትሌት ፓች ኡመድ 5 ነጥብ 95 ሜትር በመዝለል አንደኛ ሆናለች፡፡
በተመሳሳይ…
ዋይኒ ሩኒ ከፕሌይ ማውዝ ጋር ተለያየ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አሰልጣኝ ዋይኒ ሩኒ ከእንግሊዝ ሻምፒየን ሽፑ ቡድን ፕሌይ ማውዝ ጋር በስምምነት መለያየቱ ተሰምቷል፡፡
የ39 ዓመቱ የማንቼስተር ዩናይትድ የቀድሞ ኮከብ እና የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን አምበል ሩኒ÷ በተደረጉ 23 የቻምፒየን ሽፕ ጨዋታዎች 4 ጊዜ ሲያሸንፍ በ13ቱ ሽንፈት አስተናግዷል፡፡
በአሰልጣኝነት ዘመኑ ስኬት የራቀው…
ኢትዮጵያ በፎርፌ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈች
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ)በሴቶች ከ17 ዓመት በታች ማጣሪያ ኢትዮጵያ በፎርፌ ወደ ቀጣዩ ዙር አልፋለች፡፡
በሴቶች ከ17 ዓመት በታች ማጣሪያ አንደኛ ዙር ኢትዮጵያ እና ዚምባብዌ ጨዋታቸውን ለማድረግ መርሐ ግብር እንደወጣላቸው ይታወሳል።
ሆኖም ዚምባብዌ ከውድድሩ ራሷን ማግለሏን በማሳወቋ የደርሶ መልስ ጨዋታዎቹ…
ኤ ሲ ሚላን ፓውሎ ፎኔስካን ከኃላፊነት አነሳ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የጣሊያን ሴሪ ኤው ክለብ ኤ ሲ ሚላን አሰልጣኝ ፓውሎ ፎኔስካን ከኃላፊነት ማሰናበቱን ይፋ አድርጓል፡፡
ክለቡ አሰልጣኙን ያሰናበተው ኤ ሲ ሚላን በትናንትናው ዕለት ከሮማ ጋር አንድ አቻ ከተለያየ በኋላ ነው፡፡
በሴሪ ኤው እንዲሁም በአውሮፓ መድረክ ቡድኑ እያስመዘገበ ያለው ደካማ እንቅስቃሴ ለስንብቱ ምክንያት መሆኑም…
አሠልጣኝ ራውዳ ዓሊ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ አቀረቡ
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሠልጣኝ ራውዳ ዓሊ ለ23 ተጫዋቾች ጥሪ አቀረቡ፡፡
ጥሪው የቀረበው የኢትዮጵያ ከ17 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ አንደኛ ዙር ከዚምባብዌ ጋር በጥር ወር መጀመሪያ ለሚያደርገው ጨዋታ ዝግጅት ነው፡፡
በዚሁ መሠረት ጥሪ የተደረገላቸው ተጫዋቾች…
ማንቼስተር ዩናይትድ ከኒውካስትል ዩናይትድ የሚያደርጉት ግጥሚያ ይጠበቃል
አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) 19ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ-ግብሮች ሲቀጥሉ ኦልድትራፎርድ ላይ ማንቼስተር ዩናይትድ ከኒውካስል ዩናይትድ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ሆኗል፡፡
ጨዋታው ምሽት 5 ሠዓት ላይ ሲደረግ በተደጋጋሚ ሽንፈት ጫና ውስጥ የሚገኘው የሩበን አሞሪም ማንቼስተር ዩናይትድ ከኒውካስል ዩናይትድ ከባድ ፈተና ይጠብቀዋል፡፡…