Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አርሰናል ማንቼስተር ሲቲን 5 ለ 1 አሸንፏል

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሣምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አርሰናል በኤምሬትስ ስታዲየም ማንቼስተር ሲቲን 5 ለ 1 ረትቷል፡፡ የመድፈኞቹን ግቦች ኦዴጋርድ፣ ፓርቴ፣ ሌዊስ ስኬሊ፣ ሀቨርትዝ እና ንዋኔሪ ከመረብ ማሳረፍ ችለዋል፡፡ የውኃ ሰማያዊዎቹን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ ደግሞ ኤርሊንግ ሃላንድ አስቆጥሯል፡፡ ቀደም ብለው በተካሄዱ የዛሬ መርሐ-ግብሮች ማንቼስተር ዩናይትድ በክሪስታል ፓላስ እንዲሁም ብሬንትፎርድ በቶተንሃም ሆትስፐር በተመሳሳይ ውጤት 2 ለ 0 ተሸንፈዋል፡፡
Read More...

ማንቼስተር ዩናይትድ ፓትሪክ ዶርጉን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ወጣቱን ተከላካይ ፓትሪክ ዶርጉን ከጣሊያኑ ክለብ ሊቼ በ35 ሚሊየን ዩሮ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡ የ20 ዓመቱ ዴንማርካዊ ተከላካይ በዩናይትድ እስከ ፈረንጆቹ 2030 የሚያቆየውን ውል ፈርሟል። በሌላ የዝውውር መረጃ የማንቼስተር ዩናይትዱ ተጫዋች ማርከስ ራሽፎርድ አስቶን ቪላን በውሰት ለመቀላቀል…

በፕሪሚየር ሊጉ አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ24ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት 1፡30 አርሰናል ከማንቼስተር ሲቲ የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ በሊጉ ጨዋታዎች 47 ነጥቦችን በመሰብሰብ 2ኛ ደረጃ ላይ የተቀመጠው አርሰናል ከመሪው ሊቨርፑል ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ለማጥበብ ይፋለማል፡፡ በተመሳሳይ ከአርሰናል…

ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል

አዲስ አበባ፣ ጥር 25፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ18ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐግብር ከቀኑ 9 ሰዓት ቅዱስ ጊዮርጊስ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በሚደረገው በዚህ ጨዋታ 28 ነጥቦችን በመሰብሰብ በደረጃ ሰንጠረዡ ሁለተኛ ላይ የተቀመጡት ፈረሰኞቹ 22 ነጥቦችን በመሰብሰብ 7ኛ ደረጃ…

በራስ አል ኬማህ  ግማሽ ማራቶን አትሌት እጅጋየሁ ታየ አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ጥር 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በተባበሩት አረብ ኢሜሬቶች በተካሄደው የራስ አል ኬማህ የሴቶች ግማሽ ማራቶን አትሌት እጅጋየሁ ታየ ድል ቀንቷታል፡፡ እጅጋየሁ ግማሽ ማራቶኑን 1 ሰዓት ከአምስት ደቂቃ ከ52 ሴኮንድ በመጨረስ ነው ማሸነፍ የቻለችው፡፡ ኬኒያዊያኖቹ ጁዲ ኬምቦ እና ጀሲካ ቼላንጋት ሁለተኛ እና ሶስተኛ በመሆን ውድድሩን ማጠናቀቃቸውን ከአዘጋጅ…

በቻምፒዮንስ ሊግ ጥሎ ማለፍ ምድብ ሪያል ማድሪድ ከማንቼስተር ሲቲ ተደለደለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ድልድል የስፔኑ ሪያል ማድሪድ እና የእንግሊዙ ማንቼስተር ሲቲ ተገናኝተዋል። የአውሮፓ ቻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ድልድል በዛሬው ዕለት ወጥቷል። የሁለቱ ሃያላን እግር ኳስ ቡድኖች ፍልሚያ የመጀመሪያው ዙር ጨዋታ በኢትሃድ የሚካሄድ…

ቅዱስ ጊዮርጊስ ወላይታ ድቻን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ጥር 21፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 17ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ ወላይታ ድቻን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ ቀን 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደ ጨዋታ አብዱ ሳሚዮ እና አማኑኤ ኤርቦ የቅዱስ ጊዮርጊስ ግቦችን አስቆጥረዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም ፈረሰኞቹ ነጥባቸውን ወደ 28 ከፍ…