Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ኢትዮጵያ ቡና ቅዱስ ጊዮርጊስን 2 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የኢትዮጵያ ቡናን የማሸነፊያ ግቦች ዲቫይን ዋቹኩዋ እና አማኑኤል አድማሱ አስቆጥረዋል፡፡ ውጤቱን ተከትሎ ኢትዮጵያ ቡና በ59 ነጥብ 2ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ በ45 ነጥብ 7ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ ኢትዮጵያ ቡና ከሶስት ጨዋታዎች በኋላ ወደ ድል ሲመለስ ቅዱስ ጊዮርጊስ በበኩሉ ባለፉት ሶስት ጨዋታዎች ማሸነፍ አልቻለም፡፡ የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት…
Read More...

ሪያል ማድሪድ የራውል አሴንሲዮን ውል አራዘመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የስፔናዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ራውል አሴንሲዮ ከክለቡ ጋር ያለውን ውል እስከ የፈረንጆቹ 2031 ድረስ አራዝሟል፡፡ የ22 ዓመቱ የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች ራውል አሴንሲዮ በሪያል ማድሪድ እስከ 2029 የሚያቆይ ኮንትራት ቢኖረውም ለተጨማሪ ሁለት ዓመታት ለመቆየት ተስማምቷል፡፡ ሪያል ማድሪድ የተከላካይ…

ጀግናው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ …

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 6፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በርካታ ጀግና ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በዓለም ላይ በሚያደርጓቸው ውድድሮችና በሚያመጧቸው ውጤቶች የሀገራቸውን ህዝብ በደስታ ዕንባ አራጭተዋል፤ ስሜትን ከፍ ዝቅ የሚያደርጉ በርካታ አኩሪ ገድሎችንም ሰርተዋል፤ እየሰሩም ይገኛሉ። ነገር ግን እርሱ ከሁሉም ልዩ ነው ትውልድ ከትውልድ የሚቀባበላቸው ዘመን ተሻጋሪ የጀግንነት እና…

ባህር ዳር ከተማ ወላይታ ድቻን 4 ለ 0 አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ባህር ዳር ከተማ ወላይታ ድቻን 4 ለ0 አሸንፏል። ምሽት 12 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወንድወሰን በለጠ በሁለተኛው አጋማሽ ለባህር ዳር ከተማ ሦስት ግቦችን በማስቆጠር ሀትሪክ ሰርቷል። በተጨማሪም ቀሪዋን አንድ ግብ ፍፁም…

የሙሉጌታ ከበደ የቀብር ሥነሥርዓት ተፈጸመ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ከምንጊዜም ምርጥ ኢትዮጵያውያን የፊት መስመር ተጫዋቾች መካከል አንዱ የነበረው ሙሉጌታ ከበደ ቀብር ሥነሥርዓት ኮልፌ በሚገኘው የሙስሊም መካነ መቃብር ተፈፅሟል። ዛሬ ረፋድ ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም የአስክሬን ሽኝት መርሐ ግብር ከተደረገ በኋላ ቤተሰቦቹ፣ የእግር ኳስ አፍቃሪያን፣ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽንና የክለብ…

ሲዳማ ቡና እና ድሬዳዋ ከተማ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ድሬዳዋ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል። ቀን 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሀቢብ ከማል በፍጹም ቅጣት ምት በ45ኛው ደቂቃ ቀዳሚውን ግብ ለድሬዳዋ ከተማ ሲያስቆጥር÷ ሲዳማ ቡናን አቻ ያደረጋትን ግብ…

በኖርወይ ኦስሎ ዳይመንድ ሊግ አትሌት የኔዋ ንብረት አሸነፈች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኖርዌይ ኦስሎ በተካሄደው የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ዳይመንድ ሊግ ውድድር አትሌት የኔዋ ንብረት አሸንፋለች። አትሌት የኔዋ በ30 ደቂቃ 28 ሰከንድ ከ82 ማይክሮ ሰከንድ በመግባት ነው ቀዳሚ የሆነችው፡፡ አትሌት ጫልቱ ዲዳ በበኩሏ በ30 ደቂቃ 33 ሰከንድ ከ86 ማይክሮ ሰከንድ  በመግባት 3ኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቅቃለች፡፡