ስፓርት
ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ምድረ ገነት ሽረ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ምድረ ገነት ሽረ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡
ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ወጥተዋል፡፡
በጨዋታው የምድረ ገነት ሽረ ተጫዋች ስንታየሁ ወለጬ በሁለት ቢጫ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ መድን ከመቻል ይገናኛሉ፡፡
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ…
Read More...
ቼልሲ ክሪስታል ፓላስን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ መርሐ ግብር ቼልሲ ክሪስታል ፓላስን 3 ለ 1 አሸንፏል።
አመሻሽ 11፡30 ላይ በክሪስታል ፓላስ ሜዳ በተደረገው ጨዋታ የቼልሲን ግቦች ኤስቴቫኦ፣ ጆአ ፔድሮ እና፣ ኤንዞ ፈርናንዴዝ (በፍጹም ቅጣት ምት) ሲያስቆጥሩ÷ ክሪስ ሪቻርድስ የክሪስታል ፓላስን ብቸኛ ግብ ከመረብ አሳርፏል።…
ፋሲል ከነማ አርባ ምንጭ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ፋሲል ከነማ አርባ ምንጭ ከተማን 3 ለ 2 አሸነፈ።
በጨዋታው የፋሲል ከነማን ግቦች ቃልኪዳን ዘላለም (2) እና ናትናኤል ገብረጊዮርጊስ ሲያስቆጥሩ÷ የአርባምንጭ ከተማን ግቦች ታምራት ኢያሱ እና ጸጋየ አበራ (በፍጹም ቅጣት ምት) ከመረብ አገናኝተዋል።
ቀደም ሲል…
አዳማ ከተማ እና መቐለ 70 እንደርታ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አዳማ ከተማ እና መቐለ 70 እንደርታ 0 ለ 0 ተለያይተዋል።
ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም የተካሄደው ጨዋታ ያለ ምንም ግብ ነው የተጠናቀቀው።
እንዲሁም በአዲስ አበባ ስታዲያም ቀን 10 ሰዓት ላይ የተጀመረው የአርባ ምንጭ…
ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ17ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሀዲያ ሆሳዕናን 2 ለ 1 አሸንፏል።
ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን ግቦች እንዳልካቸው ጥበቡ እና ቃለአብ ውብሸት (በራሱ ላይ) አስቆጥረዋል።
በጨዋታው ሀዲያ ሆሳዕናን…
የአርሰናል የቀድሞ ተጫዋች ባካሪ ሳኛ በአዲስ አበባ..
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው የአርሰናል እና የማንቸስተር ሲቲ የቀድሞ ተጫዋች ባካሪ ሳኛ አዲስ አበባ ይገኛል፡፡
አንጋፋው ተጫዋች የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከማክሮን የትጥቅ አምራች ድርጅት ጋር የሚያደርገው የሁለትዮሽ ስምምነት አካል መሆኑ ተመላክቷል።
የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ከግብፅ ጋር ያደረገውን ጨዋታ ተመልክቻለሁ ያለው ሳኛ÷…
አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወትና አትሌት ቢቂሌ አንበሴ የ10 ኪ.ሜ የጐዳና ውድድርን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወት እና አትሌት ቢቂሌ አንበሴ የ1ኛው የኢትዮጵያ 10 ኪሎ ሜትር የጐዳና ውድድርን አሸንፈዋል።
ዛሬ ማለዳ በሐዋሳ ከተማ በተደረገው የ10 ኪሎ ሜትር የጐዳና ውድድር በወንዶች አትሌት ሀጎስ ገ/ህይወት በቀዳሚነት አጠናቅቋል።
አትሌት ሀጎስ ውድድሩን ለማጠናቀቅ 28 ደቂቃ 2 ሰከንድ ከ94 ማይክሮ…