Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

በኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር አትሌት ጌታቸውና አትሌት መሰለች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአዲስ አበባ በተካሄደው 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር በወንዶች አትሌት ጌታቸው ማስረሻ ከሸገር ሲቲ እንዲሁም በሴቶች አትሌት መሰለች አለማየሁ ከአዲስ አበባ ፖሊስ አሸንፈዋል፡፡ በወንዶች ምድብ አትሌት ባለይልኝ ተሻገር ከኢትዮ ኤሌክትሪክ 2ኛ ሲወጣ አትሌት በላይ ጥላሁን ደግሞ ከአዲስ አበባ ፖሊስ 3ኛ ደረጃን ይዟል፡፡ ውድድሩ በዴንማርክ ኮፐንሀገን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችን ለመምረጥና ተተኪዎንች ለማፍራት ያለመ ነው፡፡
Read More...

19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) 19ኛው የኢትዮጵያ ግማሽ ማራቶን ውድድር በአዲስ አበባ ከተማ መካሄድ ጀምሯል፡፡ መነሻና መድረውሻን መስቀል አደባባይ ባደረገው ውድድር በወንዶች 455፤ በሴቶች183 በድምሩ 638 አትሌቶች ተሳትፈዋል፡፡ ውድድሩ በዴንማርክ ኮፐንሀገን ለሚካሄደው የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያን የሚወክሉ አትሌቶችን ለመምረጥና…

ቶተንሃም ሆትስፐር አንዲ ሮበርትሰንን አስፈረመ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቶተንሃም ሆትስፐር ስኮትላንዳዊውን የተከላካይ ስፍራ ተጫዋች አንዲ ሮበርትሰን ወደ ስብስቡ መቀላቀሉን ይፋ አድርጓል፡፡ አንዲ ሮበርትሰን ከ9 ዓመታት የአንፊልድ ቆይታ በኋላ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከሊቨርፑል ጋር መለያየቱ ይታወሳል፡፡ ይህን ተከትሎም የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር የ32 ዓመቱን ተጫዋች በነጻ…

የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማሕበር የዓመቱ ምርጥ እጩዎች ይፋ ሆኑ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጫዋቾች ማሕበር የ2025/26 የውድድር ዓመት የዓመቱ ምርጥ እጩዎች ይፋ ሆነዋል፡፡ በዚህም አርሰናል ሦስት ተጫዋቾችን በእጩነት በማስመረጥ ቀዳሚ ሲሆን÷ ጋብሬል ማጋሌሽ፣ ዴቪድ ራያ እና ዴክላን ራይስ በእጩነት ቀርበዋል፡፡ የመድፈኞቹ ግብ ጠባቂ ዴቪድ ራያ በውድድር ዓመቱ በ19 ጨዋታዎች ግብ…

ወላይታ ድቻ እና ነገሌ አርሲ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ34ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ እና ነገሌ አርሲ ያለ ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ ሁለቱም ቡድኖች ግብ ሳያስቆጥሩ ወጥተዋል፡፡ ሊጉን ሲዳማ ቡና በ61 ነጥብ ሲመራው መቻል በ53 ነጥብ 2ኛ እንዲሁም ነገሌ አርሲ…

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አንድ ጨዋታ ይደረጋል

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ34ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ተስተካካይ መርሐ ግብር በዛሬ ዕለት ይደረጋል፡፡ በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ ወላይታ ድቻ ከነገሌ አርሲ ተስተካካይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ስታዲየም ሊደረግ መርሐ ግብር ተይዞሎት የነበረ…

አንዶኒ ኢራኦላ የሊቨርፑል አሰልጣኝ ሆኖ ተሾመ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ አንዶኒ ኢራኦላ አርነ ስሎትን በመተካት የሊቨርፑል አሰልጣኝ በመሆን ተሾሟል፡፡ በቦርንማውዝ አስደናቂ ቡድን መገንባት የቻለው ኢራኦላ በአንፊልዱ ክለብ እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆየውን ኮንትራት መፈረሙ ተገልጿል፡፡ አሰልጣኙ በቆይታው ቡድኑን ወደ አሸናፊነት የመመለስ ሃላፊነት ተጥሎበታል፡፡