Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

ወልቭስ ዌስትሃም ዩናይትድን በማሸነፍ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዘገበ  

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ወልቭስ ዌስትሃም ዩናይትድን 3 ለ 0 በማሸነፍ በሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አስመዝግቧል። ምሽት 12 ሰዓት ላይ በሜዳው ዌስትሃም ዩናይትድን ያስተናገደው ወልቭስ አሪያስ፣ ዋንግ ሂ-ቻን (በፍጹም ቅጣት ምት) እና ማኔ ባስቆጠሯቸው ግቦች ሶስት ነጥብ ይዞ ወጥቷል። ባለፈው ሳምንት ወደ ኦልድ ትራፎርድ አቅንቶ ከማንቼስተር ዩናይትድ ጋር ነጥብ ተጋርቶ የተመለሰው ወልቭስ ዛሬ ባደረገው ጨዋታ በውድድር ዘመኑ በሊጉ ለመጀመሪያ ጊዜ ለማሸነፍ በቅቷል።…
Read More...

አስቶንቪላ ኖቲንግሃም ፎረስትን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 20ኛ ሳምንት መርሐ ግብር አስቶንቪላ ኖቲንግሃም ፎረስትን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ከ30 በተረደገው ጨዋታ ኦሌ ዋትኪንስ እና ጆን ማክ ጊን (ሁለት) ለአስቶን ቪላ ግቦቹን ሲያስቆጥሩ ሞርጋን ጊብስ ዋይት የኖቲንግሃም ፎረስትን ብቸኛ ግብ ከመረብ አገናኝቷል። ውጤቱን ተክትሎም…

ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወላይታ ድቻ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 13ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ቅዱስ ጊዮርጊስ እና ወላይታ ድቻ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያተይተዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ቴዎድሮስ ሀይለማሪያም ለወላይታ ድቻ እንዲሁም አቤል ያለው ለቅዱስ ጊዮርጊስ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡…

በአፍሪካ ዋንጫ ሁለት የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ሁለት የጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች በዛሬው ዕለት ይደረጋሉ፡፡ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ሴኔጋል ከሱዳን ጋር ይገናኛሉ። በምድብ ጨዋታዎች ሴኔጋል ሁለቱን በማሸነፍ እና በአንድ ጨዋታ አቻ በመለያየት በሰባት ነጥብ ከምድቧ 1ኛ ደረጃን በመያዝ ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለች ሲሆን፤ ሱዳን…

ማንቼስተር ሲቲ ከቼልሲ …

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 25፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ20ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ መደረግ ይጀምራሉ፡፡ አስቶንቪላ ከኖቲንግሃም ፎረስት በቪላ ፓርክ ቀን 9:30 ላይ የሚያርጉት ጨዋታ ቀዳሚው መርሐ ግብር ነው፡፡ ከ11 ተከታታይ ጨዋታዎች በኋላ በሳምንቱ አጋማሽ በአርሰናል የተሸነፈው አስቶንቪላ ወደ ድል ለመመለስ ይፋለማል፡፡ ያለፉትን ሦስት…

አወዛጋቢው ኮከብ ማሪዮ ባላቶሊ…

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 24፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በነውጠኛ ባህሪው እና በአወዛጋቢ ድርጊቶቹ የሚታወቅ ተጫዋች ነው ማሪዮ ባላቶሊ፡፡ ማሪዮ ባላቶሊ ፕሮፌሽናል የእግር ኳስ ሕይወቱን የጀመረው በሀገሩ ክለብ ሉሜዛን ሲሆን÷ ከዚያ በመቀጠል ለኢንተር ሚላን፣ ማንቼስተር ሲቲ፣ ኤሲሚላን እና ሊቨርፑልን ለመሳሳሉ ታላላቅ ክለቦች መጫወቱ ይታወሳል፡፡ ከጣሊያኑ ክለብ ኢንተርሚላን…

ቼልሲ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን አሰናበተ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 23፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ቼልሲ አሰልጣኝ ኢንዞ ማሬስካን አሰናብቷል፡፡ የክለቡ ቦርድ በአሰልጣኙ ቆይታ ዙሪያ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የጣሊያናዊው አሰልጣኝ ውል እንዲቋረጥ ወስኗል፡፡ እስከ ፈረንጆቹ 2029 በክለቡ የሚያቆይ ውል የነበራቸው ኢንዞ ማሬስካ በስምምነት ከክለቡ ጋር መለያየታቸውን ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡