ስፓርት
ኦስማን ዴምቤሌ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመረጠ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ፈረንሳዊው የፒኤስጂ የፊት መስመር ተጫዋች ኦስማን ዴምቤሌ የ2024/25 አውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የውድድሩ ምርጥ ተጫዋች ተብሎ ተመርጧል፡፡
የ28 ዓመቱ ዴምቤሌ በውድድር ዓመቱ ባደረጋቸው 15 የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ጨዋታዎች፤ 8 ጎል አስቆጥሮ 6 ለግብ የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ ማቀበል ችሏል፡፡
ፒኤስጂ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ሲያሳካ የዴምቤሌ አስተዋፅኦ የጎላ ነበር፡፡
ፒኤስጂ በፍፃሜው ኢንተርሚላንን 5 ለ 0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ሻምፒየን መሆኑ…
Read More...
ማንቼስተር ዩናይትድ ማቲውስ ኩንሀን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን የፊት መስመር ተጫዋች ማቲውስ ኩንሀን ከወልቭስ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
የ26 ዓመቱ ማቲውስ ኩንሀ በማንቼስተር ዩናይትድ ቤት በፈረንጆቹ እስከ 2030 የሚያቆውን ውል ፈርሟል፡፡
ከአምሥት ዓመት ውሉ ባሻገር ለአንድ ዓመት የማራዘም ተጨማሪ አማራጭ መኖሩ በፊርማ ሥነ-ሥርዓቱ…
ኢትዮጵያ ቡና የ100 ሺህ ብር ቅጣት ተጣለበት
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በኢትዮጰያ ፕሪሚየር ሊግ 32ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ጨዋታ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች በአዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባጠፉት ጥፋት ክለቡ የ100 ሺህ ብር ቅጣት ተላልፎበታል፡፡
ኢትዮጵያ ቡና ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ጋር ያደረገውን የ32ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ያለምንም ግብ…
ሀዋሳ ከተማ መቻልን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 23፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሀዋሳ ከተማ መቻልን 3 ለ 1 አሸንፏል።
የሀዋሳ ከተማን ማሸነፊያ ግቦች አሊ ሱሌማን፣ ተባረክ ሄፋሞ እና አቤኔዘር ዮሐንስ አስቆጥረዋል።
መቻልን ከመሸነፍ ያልታደገውን ብቸኛ ግብ ምንይሉ ወንድሙ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል።
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ…
ድሬዳዋ ከተማ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) በ32ኛ ሳምንት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ድሬዳዋ ከተማ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡
የድሬዳዋ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ዮሀንስ ደረጀ እና እስማኤል አብዱል ጋንዩ ሲያስቆጥሩ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ ቢንያም ካሳሁን ከመረብ አሳርፏል፡፡
ድሬዳዋ ከተማ ተከታታይ…
ኢስትቫን ኮቫክስ የነገ ምሽቱን የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ይመራሉ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አሊያንዝ አሬና ስታዲየም ነገ ምሽት የሚደረገውን የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታ ሮማኒያዊው ዳኛ ኢስትቫን ኮቫክስ በመሀል ዳኝነት ይመሩታል፡፡
የመሀል ዳኛው ኢስትቫን ኮቫክስ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ፣ ዩሮፓ ሊግ እና ኮንፈረንስ ሊግ የፍፃሜ ጨዋታዎችን በመሀል ዳኝነት የመሩ የመጀመሪያው ሰው ይሆናሉ።…
ሪያል ማድሪድ አሌክሳንደር አርኖልድን አስፈረመ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 22፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ኃያል ክለብ ሪያል ማድሪድ ትሬንት አሌክሳንደር አርኖልድን ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
አሌክሳንደር አርኖልድ በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ከልጅነት ክለቡ ሊቨርፑል ለመልቀቅ መወሰኑን ከሣምንታት በፊት ማሳወቁ ይታወሳል፡፡
በወቅቱም፤ ራሱን በአዲስ ክለብ እና በተለየ ቦታ ለመፈተሽ በመፈለጉ ከሊቨርፑል ለመልቀቅ…