Fana: At a Speed of Life!

ስፓርት

አንጎላ እና ዚምባቡዌ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታ ዛሬ ቀጥሎ ሲካሄድ ቀን 9 ሰዓት የተገናኙት አንጎላ እና ዚምባቡዌ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል። ጄልሰን ዳላ ለአንጎላ እንዲሁም ኖሌጅ ሙሶና ለዚምባቡዌ ግቦቹን አስቆጥረዋል። ጨዋታው ቀጥሎ ሲካሄድ ግብጽ እና ደቡብ አፍሪካ ምሽት 12 ሰዓት የሚያደርጉት ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ ምሽት 2 ሰዓት ከ30 በምድብ አንድ የሚገኙት ዛምቢያ ከኮሞሮስ እንዲሁም ምሽት 5 ሰዓት አዘጋጇ ሞሮኮ ከማሊ ጋር ይጫወታሉ።
Read More...

መቻል አዳማ ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ11ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ መቻል አዳማ ከተማን 3 ለ 1 አሸንፏል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የመቻልን ግቦች መሀመድ አበራ (2) እና በረከት ደስታ አስቆጥረዋል፡፡ አዳማ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን ብቸኛ ግብ አህመድ ሁሴን ከመረብ አሳርፏል፡፡…

ማንቼስተር ዩናይትድ ከኒውካስል ዩናይትድ…

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ18ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት ማንቼስተር ዩናይትድ ከኒውካስል ዩናይትድ ይጫወታሉ፡፡ ያለፉትን ተከታታይ ሁለት የፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ማሸነፍ ያልቻሉት ሁለቱም ክለቦች ወደ ድል ለመመለስ ዛሬ ምሽት 5 ሰዓት በኦልድትራፎርድ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ ሁለቱ ቡድኖች በፕሪሚየር ሊጉ እርስ…

በአፍሪካ ዋንጫ የምድብ ማጣሪያ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 17፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በሞሮኮ እየተካሄደ በሚገኘው 35ኛው የዐፍሪካ ዋንጫ በዛሬው ዕለት አራት የምድብ ሁለተኛ ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡ አዘጋጇ ሞሮኮ ከማሊ እንዲሁም ግብፅ ከደቡብ አፍሪካ የሚያደርጉት ጨዋታ ተጠባቂ ነው፡፡ በዕለቱ የመጀመሪያ መርሐ ግብር በምድብ ሁለት የሚገኙት አንጎላ እና ዚምባቡዌ ቀን 9 ሰዓት ከ30 ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡…

ሀዋሳ ከተማ ሸገር ከተማን አሸነፈ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ11ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሀዋሳ ከተማ ሸገር ከተማን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የሀዋሳ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች ያሬድ ብሩክ እና ጌታነህ ከበደ አስቆጥረዋል፡፡ ሸገር ከተማን ከሽንፈት ያልታደገችዋን…

የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል በጅማ ዩኒቨርሲቲ ይካሄዳል

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የዘንድሮው የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስፖርት ፌስቲቫል "ስፖርት ብዝሃነትና እወቀት ለልህቀት" በሚል መሪ ሃሳብ ከጥር 9 እስከ 24 በጅማ ዩኒቨርሲቲ ይካሄዳል፡፡ በፌስቲቫሉ በሁለቱም ጾታ በ15 የስፖርት አይነቶች ውድድሮች የሚካሄዱ ሲሆን፥ የስታዲየም፣ የመዋኛ ገንዳ እድሳትን ጨምሮ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት መጠናቀቁን…

ለ17ኛ ተከታታይ ጊዜ በአፍሪካ ዋንጫ እየተሳተፈች የምትገኘው ቱኒዚያ

አዲስ አበባ፣ ታሕሣሥ 16፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአፍሪካ ዋንጫ ታሪክ ለበርካታ ተከታታይ ዓመታት በመድረኩ በመሳተፍ ቀዳሚዋ ሀገር ናት ቱኒዚያ፡፡ በ35ኛው የሞሮኮ የአፍሪካ ዋንጫ በታሪኳ ለ21ኛ ጊዜ እየተሳተፈች የምትገኘው ቱኒዚያ ለ17ኛ ተከታታይ ጊዜ በአህጉሪቱ ትልቁ መድረክ ላይ ተገኝታለች፡፡ በፈረንጆቹ 1956 ነጻነቷን ከፈረንሳይ ያገኘችው ቱኒዚያ የእግር ኳስ…