Fana: At a Speed of Life!

በአሸባሪው ሸኔ ምክንያት በኦሮሚያ ክልል ከ325 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ ሆነዋል

በላይ

አዲስ አበባ፣ ጥር 17፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል 163 ትምህርት ቤቶች በሸኔ ታጣቂዎች መቃጠላቸውን እና 756 ትምህርት ቤቶች መዘረፋቸውን የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ገለፁ።

የቢሮው ሃላፊ አቶ ኃይሉ አዱኛ እንደገለፁት፥ በአሸባሪው ሸኔ ምክንያት ትምህርት ቤቶች ላይ በደረሰው ውድመት 325 ሺህበላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ሆነዋል።

በተጨማሪም 5 ሺህ 227 መምህራን ከሥራ ውጪ መሆናቸውን ነው ያመለከቱት።
በሌላ በኩል ክልሉ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ለማጠናከር በሠራው ሥራ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 23 ትምህርት ቤቶች በኦሮሚኛ ቋንቋ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑን ሃላፊው ገልጸዋል፡፡
በአማራ ክልል ከሚሴ ዞን፣ በጋምቤላ ክልል እና በሌሎች ክልሎችም የአፋን ኦሮሞ ትምህርት እየተሰጠ መሆኑም ተመላክቷል፡፡

ምንም እንኳን አሸባሪው ሸኔ ኢ-ሠብዓዊ በሆነ መንገድ በትምህርት ተቋማት ላይ ውድመቶችን ቢፈጽምም፥ በክልሉ በኢፋቦሩ ፕሮጀክት ባለፈው አንድ ዓመት ከ100 በላይ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባት ታቅዶ 93 የሚሆኑት ከ2 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ ተገንብተው የመማር ማስተማር ሥራ መጀመራቸውን ሀላፊው ተናግረዋል።

በክልሉ ሰባት አዳሪ ትምህርት ቤቶችም መገንባታቸውን ነው ያመለከቱት፡፡

በገመቹ ቤኩማ
ኢትዮጵያን፦ እናልማ፣ እንገንባ፣ እንዘጋጅ
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
You might also like

Leave A Reply

Your email address will not be published.